የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በተጠናቀቀው በጀት አመት ህብረተሰቡ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል

Jul 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፦በ2017 በጀት አመት ህብረተሰቡ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ገለፀ።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመንግስትና በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነባ መሆኑም ተገልጿል።

በ2017 በጀት ዓመት ህብረተሰቡ ለግድቡ ግንባታ ያደረገውን ድጋፍ፣ ትብብርና እገዛ በተመለከተ የጽህፈት ቤቱ ምክትል ስራ አስፈጻሚ ፍቅርተ ተአምር ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የተፋሰሱ ሀገራት ህዝቦችን በጋራ የማደግ ትልምን የሚያሳካ ፕሮጀክት መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህም መላው ኢትዮጵያውያን በሞራል፣ በገንዘብ፣ በጉልበት፣ በፐብሊክ ዲፕሎማሲ እንዲሁም አካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ያሳኩት ዘመን ተሻጋሪ ስኬት መሆኑንም አስረድተዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ አልፎ የአካባቢውን ሀገራት የኤሌትሪክ ሃይል ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት መሆኑንም አክለዋል።

ምክትል ስራ አስፈፃሚዋ ከቦንድ ሽያጭና ስጦታ፣ ከዲያስፖራው ማህበረሰብ፣ ከ8100 A አጭር የፅሁፍ መልዕክት ድጋፉ መሰባሰቡንም ጠቅሰዋል።

በዚህም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለግድቡ ግንባታ 1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር መሰብሰቡን ገልጸው፤ ይህም ከዕቅዱ አንጻር የ7 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል፡፡

ህብረተሰቡ ያደረገው ድጋፍ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር አፈፃፀሙ የ21 በመቶ ብልጫ ማሳየቱንም ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025