የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባቸው አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከልና ወርክሾፖች አገልግሎት አሰጣጡን የሚያሳድጉ ናቸው

Jul 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባቸው አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከልና ወርክሾፖች አገልግሎት አሰጣጡን የሚያሳድጉ መሆናቸውን የኢፌዲሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ተጨማሪ አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከል እንዲሁም ወርክሾፖችን ዛሬ አስመርቋል።


በምረቃ መርሃ ግብሩ የኢፌዲሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰውና የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

ማዕከላቱ የአየር መንገዱ እና ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ አውሮፕላኖች ጥገና እና እድሳት የሚካሄድባቸው መሆኑ ተገልጿል።

የተገነቡት የአውሮፕላን ክፍሎች የማዕከላዊ መጋዘን እና የአውሮፕላን ክፍሎች ወርክሾፕ የተለያዩ የአውሮፕላን ክፍሎች በቴክኖሎጂ በታገዘ አሰራር ተደራጅተው የሚቀመጡበት መሆኑ ተገልጿል።

በዛሬው እለት የተመረቁት መሰረተ ልማቶች ከአየር መንገዱ የራእይ 2035 ግቦች ውስጥ አንዱ መሆኑም ተመልክቷል።

የኢፌዲሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ማእከላቱ የአየር መንገዱን የእድገት ከፍታ የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

እንዲሁም አየር መንገዱ ያለውን የረጅም ጊዜ ራእይ የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰው፤ መሰረተ ልማቱ ቀጣይነት ላለው የእድገት ጉዞ ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።


በዛሬው እለት የተመረቁ ማእከላትም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጉ መሆናቸውን አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፥ ማእከላቱ የአየር መንገዱን አገልግሎት አሰጣጥ የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል።

ግንባታቸውን ለማጠናቀቅ ሁለት አመት መፍጀቱን ገልጸው፤ ተጨማሪ አቅም በመፍጠር ገቢን ለማሳደግም ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።

እንዲሁም የማእከላዊ መጋዘኑም የእድሳት እና ጥገና ስራውን የሚያቀላጥፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ አየር መንገዱ የእድገት ጉዞውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026