የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባቸው አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከልና ወርክሾፖች አገልግሎት አሰጣጡን የሚያሳድጉ ናቸው

Jul 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያስገነባቸው አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከልና ወርክሾፖች አገልግሎት አሰጣጡን የሚያሳድጉ መሆናቸውን የኢፌዲሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ገለጹ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ተጨማሪ አዳዲስ የአውሮፕላን ጥገና፣ የእድሳት ማዕከል እንዲሁም ወርክሾፖችን ዛሬ አስመርቋል።


በምረቃ መርሃ ግብሩ የኢፌዲሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰውና የአየር መንገዱ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

ማዕከላቱ የአየር መንገዱ እና ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ አውሮፕላኖች ጥገና እና እድሳት የሚካሄድባቸው መሆኑ ተገልጿል።

የተገነቡት የአውሮፕላን ክፍሎች የማዕከላዊ መጋዘን እና የአውሮፕላን ክፍሎች ወርክሾፕ የተለያዩ የአውሮፕላን ክፍሎች በቴክኖሎጂ በታገዘ አሰራር ተደራጅተው የሚቀመጡበት መሆኑ ተገልጿል።

በዛሬው እለት የተመረቁት መሰረተ ልማቶች ከአየር መንገዱ የራእይ 2035 ግቦች ውስጥ አንዱ መሆኑም ተመልክቷል።

የኢፌዲሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቦርድ ሊቀመንበር ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ማእከላቱ የአየር መንገዱን የእድገት ከፍታ የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።

እንዲሁም አየር መንገዱ ያለውን የረጅም ጊዜ ራእይ የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰው፤ መሰረተ ልማቱ ቀጣይነት ላለው የእድገት ጉዞ ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።


በዛሬው እለት የተመረቁ ማእከላትም በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርጉ መሆናቸውን አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፥ ማእከላቱ የአየር መንገዱን አገልግሎት አሰጣጥ የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል።

ግንባታቸውን ለማጠናቀቅ ሁለት አመት መፍጀቱን ገልጸው፤ ተጨማሪ አቅም በመፍጠር ገቢን ለማሳደግም ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።

እንዲሁም የማእከላዊ መጋዘኑም የእድሳት እና ጥገና ስራውን የሚያቀላጥፍ መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይ አየር መንገዱ የእድገት ጉዞውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026