
ሆሳዕና፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በየዘርፉ የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ።
"ከመስፈንጠር ከፍታ ወደ ላቀ እመርታ!” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የመንግሥትና የፓርቲ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ላይ ያተኮረ የአመራር ምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳመለከቱት፤ ባለፈው የበጀት ዓመት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተያዙ እቅዶችን በቅንጅት በመስራት ተስፋ ሰጪ ውጤት ተመዝግቧል፡፡
በዚህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኑሮ ውድነትን ከማረጋጋት ባሻገር በከተማና በገጠር መንገድ ተደራሽ እንዲሆን የተደረገውን ጥረት ጠቅሰዋል።
ለወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አንጻር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
ይህም በክልሉ በበጀት ዓመቱ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ስራዎች በትክክለኛ መንገድ ላይ እንደሚገኙ አንስተዋል።
በተያዘው የበጀት ዓመት መልካም አስተዳደርን በማስፈን ፍትሀዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለተገልጋዩ ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ተናግረዋል።
የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል በየዘርፉ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ አመራሩ በቅንጅት መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡
በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)፥ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በፓርቲ ደረጃ ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በዚህም በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
ባለፈው የበጀት ዓመት የተስተዋሉ ውስንነቶችን በማረም የሕዝብ ተጠቃሚነትን ይበልጥ ለማጎልበት በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ እንዳሉት፤ በዞኑ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በግብርና ልማት፣ በንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና በሌሎችም ዘርፎች ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል።
በመድረኩ ላይ ካለፈው የስራ ዘመን እቅድ አፈጻጸም ሌላ የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ምክክር የተደረገ ሲሆን ፤ በዚህም የክልል፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026