የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ- ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር)

Jul 23, 2025

IDOPRESS

ሆሳዕና፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በየዘርፉ የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው(ዶ/ር) ገለጹ።

"ከመስፈንጠር ከፍታ ወደ ላቀ እመርታ!” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የመንግሥትና የፓርቲ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ላይ ያተኮረ የአመራር ምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ተካሂዷል፡፡


በመድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳመለከቱት፤ ባለፈው የበጀት ዓመት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተያዙ እቅዶችን በቅንጅት በመስራት ተስፋ ሰጪ ውጤት ተመዝግቧል፡፡

በዚህም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የኑሮ ውድነትን ከማረጋጋት ባሻገር በከተማና በገጠር መንገድ ተደራሽ እንዲሆን የተደረገውን ጥረት ጠቅሰዋል።

ለወጣቶች የስራ እድል ከመፍጠር አንጻር የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ይህም በክልሉ በበጀት ዓመቱ የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ስራዎች በትክክለኛ መንገድ ላይ እንደሚገኙ አንስተዋል።

በተያዘው የበጀት ዓመት መልካም አስተዳደርን በማስፈን ፍትሀዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለተገልጋዩ ለመስጠት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ተናግረዋል።

የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ በማስቀጠል በየዘርፉ የሕዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ አመራሩ በቅንጅት መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል፡፡

በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዲላሞ ኦቶሬ (ዶ/ር)፥ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በፓርቲ ደረጃ ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል፡፡

በዚህም በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።

ባለፈው የበጀት ዓመት የተስተዋሉ ውስንነቶችን በማረም የሕዝብ ተጠቃሚነትን ይበልጥ ለማጎልበት በትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ከመድረኩ ተሳታፊዎች መካከል የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ እንዳሉት፤ በዞኑ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት በግብርና ልማት፣ በንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና በሌሎችም ዘርፎች ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል።

በመድረኩ ላይ ካለፈው የስራ ዘመን እቅድ አፈጻጸም ሌላ የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ምክክር የተደረገ ሲሆን ፤ በዚህም የክልል፣ የዞን፣ የልዩ ወረዳና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025