
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የቢሾፍቱ ግብርና ምርምር ማዕከል የእንስሳት ዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ የሚያስችሉ የምርምር ውጤቶችን እያሰራጨ መሆኑን ገለፀ።
ማዕከሉ በተለያዩ ሰብልና እንስሳት ላይ ከ70 ዓመታት በላይ ምርምር በማድረግ ዝርያዎችን የማሻሻል ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል።

በማዕከሉ የብሄራዊ ዶሮ ምርምር ፕሮግራም አስተባባሪ ሚስባህ አለዊ ለ15 አመት ከተዘጋጀው የዶሮ ምርምር ስትራቴጂ ከተቀዱ ስድስት የምርምር የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል ሶስቱ ዝርያ ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ማዕከሉ ለዶሮ አርቢዎችና ለተለያዩ አካላት ስልጠና ከመስጠት ባለፈ የአንድ ቀን ጫጩት አባዝቶ ለአርሶ አደሮች እያሰራጨ ይገኛል ብለዋል።

ከውጭ የሚገቡና ለኮሜርሺያል ዶሮ እርባታ ተስማሚ ዝርያዎችን የመፈተሽ፣ ሀገር በቀል የዶሮ ዝርያን ማሻሻልና ከውጭ የሚገቡ ዝርያዎችን በመጠቀም ለአርሶ አደሮች የሚሆኑ ዝርያዎችን የማልማት ስራ እየሰራ ነው ብለዋል።
የሆሮ ሀገር በቀል ዶሮ ዝርያ በመረጣ የማሻሻል፣ ከውጭ የገቡ ሶስት ዝርያዎችን በማዳቀል ዲዜድ የተሰኘ ዝርያ በምርምር መውጣቱን ገልፀዋል።
በማዕከሉ የብሄራዊ እንስሳት ባዮቴክኖሎጂ ምርምር ፕሮግራም አስተባባሪ ሰኢድ አሊ ማዕከሉ በእንስሳት ዘርፉ ላይ የተለያዩ ምርምሮችን የመስራትና የማስተባበር እንዲሁም የእንስሳት ስነተዋልዶ ባዮቴክኖሎጂ ላይ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በዚህም በሰው ሰራሽ ዘዴ ማዳቀል(አርቲፊሻል ኢንሲሜሽን)፣ የኮርማ ፍላጎት ማቀናጀት እንዲሁም ፆታው የተለየ የኮርማ አባላዘር ቴክኖሎጂ የመጠቀም ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በዚህም ላለፉት ሶስት አመታት የወተት መንደሮችን በመመስረት ከ600 በላይ ጥጆች መወለዳቸውን ተናግረዋል።
የፅንስ ዝውውርና በላቦራቶሪ ፅንስ የመፍጠር ስራ ማዕከሉ በእንስሳት ስነተዋልዶ ባዮቴክኖሎጂ ዘርፍ ከሚያከናውናቸው ስራዎች መካከል እንደሚገኙበት አስረድተዋል።
በማዕከሉ የእንስሳት ፕሮግራም አስተባባሪ ካሰች መለሰ እንዳሉት በማዕከሉ ለተሻሻሉ ዝርያዎች የሚመጥኑ የመኖ ልማት ጥናቶች እየተሰሩ ይገኛሉ።

በመኖና ስነ-ምግብ ምርምር የተለያዩ የመኖ ዘሮችን በመፈተሽ አርሶ አደሮች እንዲጠቀሙበት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026