
ወልቂጤ፣ ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፡-የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክትትልና ድጋፍ ተግባሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያጎለበቱ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ መስራቱን የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ።
ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን በወልቂጤ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል ።

በጉባኤ መክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ እንደገለፁት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ምክር ቤቱ ተከታታይነት ያለው መደበኛ እና ድንገተኛ የክትትል፣ የቁጥጥርና ድጋፍ ሥራዎች ሲያከናውን ቆይቷል።
በዚህም በክልሉ በፖለቲካዊ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ የተሻለ ለውጥ እንዲመጣ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ሲወጣ መቆየቱን አንስተዋል።
የመንገድ፣ የውሃ፣ የመስኖ እና የጤናን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ ተቋማት ተግባርን የመከታተል፣ የማረምና የመደገፍ ስራ ማከናወኑንም ተናግረዋል ።
በዓመቱ በክልሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ጀምሮ የመጨረስና የተጓተቱትን አጠናቅቆ ወደ አገልግሎት ከማስገባት አንጻር የተሻለ አፈጻጸምና ልምድ እየታየ መምጣቱን ምክር ቤቱ ማረጋገጡን አንስተዋል።
በዚህም ክልሉ ከተመሰረተ አጭር ጊዜ ቢሆንም ተጓተው የነበሩ ሰፋፊ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ በትኩረት መሰራቱን ነው አፈ-ጉባኤዋ የተናገሩት።
በቀጣይም ለሰላም ግንባታ፣ ለልማት እና ለመልካም አስተዳደር ሥራዎች ውጤታማነትና ተፈጻሚነት ምክር ቤቱ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ዛሬ በተጀመረው የዓመቱ ማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤም ምክር ቤቱ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አፌ-ጉባኤዋ ጠቁመዋል።
የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት እንደሚካሄድ ታውቋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025