የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የክልሉ ምክር ቤት በክትትልና ድጋፍ ተግባሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያጎለበቱ ሥራዎች እንዲከናወኑ ሰርቷል

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፣ ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፡-‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክትትልና ድጋፍ ተግባሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያጎለበቱ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ መስራቱን የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ።

‎ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን በወልቂጤ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል ።


በጉባኤ መክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት ‎የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ እንደገለፁት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ምክር ቤቱ ተከታታይነት ያለው መደበኛ እና ድንገተኛ የክትትል፣ የቁጥጥርና ድጋፍ ሥራዎች ሲያከናውን ቆይቷል።

በዚህም በክልሉ በፖለቲካዊ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ የተሻለ ለውጥ እንዲመጣ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ሲወጣ መቆየቱን አንስተዋል።

የመንገድ፣ የውሃ፣ የመስኖ እና የጤናን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ ተቋማት ተግባርን የመከታተል፣ የማረምና የመደገፍ ስራ ማከናወኑንም ተናግረዋል ።

በዓመቱ በክልሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ጀምሮ የመጨረስና የተጓተቱትን አጠናቅቆ ወደ አገልግሎት ከማስገባት አንጻር የተሻለ አፈጻጸምና ልምድ እየታየ መምጣቱን ምክር ቤቱ ማረጋገጡን አንስተዋል።

‎በዚህም ክልሉ ከተመሰረተ አጭር ጊዜ ቢሆንም ተጓተው የነበሩ ሰፋፊ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ በትኩረት መሰራቱን ነው አፈ-ጉባኤዋ የተናገሩት።

በ‎ቀጣይም ለሰላም ግንባታ፣ ለልማት እና ለመልካም አስተዳደር ሥራዎች ውጤታማነትና ተፈጻሚነት ምክር ቤቱ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

ዛሬ በተጀመረው የዓመቱ ማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤም ‎ምክር ቤቱ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አፌ-ጉባኤዋ ጠቁመዋል።

የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት እንደሚካሄድ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025