የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የክልሉ ምክር ቤት በክትትልና ድጋፍ ተግባሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያጎለበቱ ሥራዎች እንዲከናወኑ ሰርቷል

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፣ ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፡-‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክትትልና ድጋፍ ተግባሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያጎለበቱ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ መስራቱን የምክር ቤቱ ዋና አፈ-ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ ገለጹ።

‎ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን በወልቂጤ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል ።


በጉባኤ መክፈቻው ላይ ንግግር ያደረጉት ‎የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ እንደገለፁት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ምክር ቤቱ ተከታታይነት ያለው መደበኛ እና ድንገተኛ የክትትል፣ የቁጥጥርና ድጋፍ ሥራዎች ሲያከናውን ቆይቷል።

በዚህም በክልሉ በፖለቲካዊ፣ በማህበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ላይ የተሻለ ለውጥ እንዲመጣ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ሲወጣ መቆየቱን አንስተዋል።

የመንገድ፣ የውሃ፣ የመስኖ እና የጤናን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ ተቋማት ተግባርን የመከታተል፣ የማረምና የመደገፍ ስራ ማከናወኑንም ተናግረዋል ።

በዓመቱ በክልሉ የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን ጀምሮ የመጨረስና የተጓተቱትን አጠናቅቆ ወደ አገልግሎት ከማስገባት አንጻር የተሻለ አፈጻጸምና ልምድ እየታየ መምጣቱን ምክር ቤቱ ማረጋገጡን አንስተዋል።

‎በዚህም ክልሉ ከተመሰረተ አጭር ጊዜ ቢሆንም ተጓተው የነበሩ ሰፋፊ የልማት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ስራ እንዲገቡ በትኩረት መሰራቱን ነው አፈ-ጉባኤዋ የተናገሩት።

በ‎ቀጣይም ለሰላም ግንባታ፣ ለልማት እና ለመልካም አስተዳደር ሥራዎች ውጤታማነትና ተፈጻሚነት ምክር ቤቱ የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

ዛሬ በተጀመረው የዓመቱ ማጠቃለያ መደበኛ ጉባኤም ‎ምክር ቤቱ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አፌ-ጉባኤዋ ጠቁመዋል።

የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት እንደሚካሄድ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026