
ባህር ዳር፣ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ጎንደር ዞን ሰላምን በማፅናት ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ተግባራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ ጌትነት በዛ ለኢዜአ እንደገለጹት፤በየደረጃው የሚገኘው የዞኑ ሕዝብ የፅንፈኛውን ቡድን የጥፋት መንገድ አደባባይ ወጥቶ ከማውገዝ ባለፈ የህግ የበላይነት እንዲከበር የድርሻውን መወጣቱን ቀጥሏል።
ተከታታይ ህዝባዊ መድረኮች በመፍጠር ቡድኑን ከሕህዝቡ የመነጠል ስራ መከናወኑን አውስተዋል።
በዞኑ የሰፈነውን ሰላምና መረጋጋት በማስጠበቅ የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያግዙ ውጤታማ ሰራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።
መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ ወደ ሰላም የመጡ በርካታ ታጣቂዎችን የተሃድሶ ስልጠና በመውሰድ ሕብረተሰቡን በልማት እንዲክሱ እየተደረገ ነው ብለዋል።
ፅንፈኛውን ቡድን ከዞኑ ለማፅዳት ከመከላከያ ሰራዊቱና ከሌሎችም የህግ አስከባሪዎች ጋር በመተባበር እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተዋል።
በተወሰደበት እርምጃ ፅንፈኛው እየታደከመ መምጣቱን ገልጸው፤ ይህም ለግብርና ልማቱ ግብአት ለማቅረብና ባለሙያዎች ተንቀሳቅሰው አርሶ አደሩን እንዲደግፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል።
ቀሪ የፅንፈኛውን ቡድን አባላት በየጊዜው የሰላም አማራጭን በመቀበል አሁንም እየተመለሱ መሆኑም አመልክተዋል።
የተገኘውን ሰላም በማፅናት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር አስቻይ መደላደል መፈጠሩን ኃላፊው አስታውቀዋል።
መንግስት አሁንም በሰላማዊ መንገድ ለሚመጡ ታጣቂዎች እጁ የተዘረጋ መሆኑን ጠቁመው፤ ይሄን በማይቀበሉት ላይ ደግሞ ከሕዝቡ ጋር በመተባበር የህግ ማስከበር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026