የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በዞኑ ሰላምን በማፅናት ለልማት ተግባራት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሯል

Jul 24, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፣ሐምሌ 16/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ጎንደር ዞን ሰላምን በማፅናት ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ተግባራት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን የዞኑ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ጌትነት በዛ ለኢዜአ እንደገለጹት፤በየደረጃው የሚገኘው የዞኑ ሕዝብ የፅንፈኛውን ቡድን የጥፋት መንገድ አደባባይ ወጥቶ ከማውገዝ ባለፈ የህግ የበላይነት እንዲከበር የድርሻውን መወጣቱን ቀጥሏል።

ተከታታይ ህዝባዊ መድረኮች በመፍጠር ቡድኑን ከሕህዝቡ የመነጠል ስራ መከናወኑን አውስተዋል።

በዞኑ የሰፈነውን ሰላምና መረጋጋት በማስጠበቅ የሕብረተሰቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያግዙ ውጤታማ ሰራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።

መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተከትሎ ወደ ሰላም የመጡ በርካታ ታጣቂዎችን የተሃድሶ ስልጠና በመውሰድ ሕብረተሰቡን በልማት እንዲክሱ እየተደረገ ነው ብለዋል።

ፅንፈኛውን ቡድን ከዞኑ ለማፅዳት ከመከላከያ ሰራዊቱና ከሌሎችም የህግ አስከባሪዎች ጋር በመተባበር እርምጃ እየተወሰደ መሆኑን አንስተዋል።

በተወሰደበት እርምጃ ፅንፈኛው እየታደከመ መምጣቱን ገልጸው፤ ይህም ለግብርና ልማቱ ግብአት ለማቅረብና ባለሙያዎች ተንቀሳቅሰው አርሶ አደሩን እንዲደግፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል።

ቀሪ የፅንፈኛውን ቡድን አባላት በየጊዜው የሰላም አማራጭን በመቀበል አሁንም እየተመለሱ መሆኑም አመልክተዋል።

የተገኘውን ሰላም በማፅናት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር አስቻይ መደላደል መፈጠሩን ኃላፊው አስታውቀዋል።

መንግስት አሁንም በሰላማዊ መንገድ ለሚመጡ ታጣቂዎች እጁ የተዘረጋ መሆኑን ጠቁመው፤ ይሄን በማይቀበሉት ላይ ደግሞ ከሕዝቡ ጋር በመተባበር የህግ ማስከበር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025