
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 16/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ቁርጠኛ ናት ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ ገለጹ።
ከልኡክ ቡድናቸው ጋር በድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ጄኔቫ የሚገኙት ሚኒስትር ዴኤታው ከጉባኤው ጎን ለጎን ከዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ንጎዚ ኦኮንጆ ኢዋላ(ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም ኢትዮጵያ የድርጅቱ አባል ለመሆን ቁርጠኛ መሆንዋንና እየተከናወኑ ያሉ ጥረቶችን እንዲሁም ለ6ኛው የስራ ቡድን ስብሰባ ያላትን ዝግጁነት አብራርተዋል፡፡
የዓለም ንግድ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው ለረጅም ጊዜ የቆየውንየኢትዮጵያን የአባልነት ድርድር ለማጠናቀቅ በሁሉም ደረጃ ባሉ የመንግስት አካላት ያለው ቁርጠኝነት አስተማማኝ መሆኑን ገልጸዋል።
ድርድሩን በታቀደለት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ይህንኑ ፍጥነትና ትጋት ማስቀጠል እንደሚገባም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የአባልነት ድርድር 6ኛው ዙር የስራ ቡድን ስብሰባ በመስከረም ወር መጨረሻ ላይ እንዲካሄድ ስምምነት ላይ የተደረሰ መሆኑ ተገልጿል።
አስቀድሞ በታቀደው መሰረትም የድርድር ሂደቱን እ.ኤ.አ ማርች 2026 ዓ.ም በካሜሩን /ያውንዴ/ በሚካሄደው የድርጅቱ የሚኒስትሮች ጉባኤ ላይ ለማጠናቀቅ ያለማቋረጥ እንደሚቀጥል መነጋገራቸውን ኢዜአ ከስፍራው ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025