የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለውጭ ገበያ ለሚቀርቡ ሰሊጥና አኩሪ አተር ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

Jul 25, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለውጭ ገበያ ለሚቀርቡ የሰሊጥና አኩሪ አተር ልማት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ የክረምት መግባትን ተከትሎ በተሰራው ሥራ እስካሁን 500 ሺህ ሄክታር መሬት በሰሊጥና በአኩሪ አተር ሰብሎች በዘር መሸፈኑ ተመልክቷል።


በቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በክልሉ ለኢንዱስትሪ ግብአትና ለወጪ ንግድ የሚሆኑ ሰብሎችን ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

በዚህም በ2017/18 የምርት ዘመን 781 ሺህ ሄክታር መሬት በአኩሪ አተርና ሰሊጥ ሰብሎች ለመሸፈን ታቅዶ በተሰራው ስራ እስካሁን ድረስ 500 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ተችሏል ብለዋል።

ከዕቅዱ ጋር ሲነጻጸርም ያልታረሰ ቀሪ መሬት እንዳለ ገልጸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁሉንም መሬት በመዝራት ወደ አረምና እንክብካቤ ሥራ ለመግባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ የምርት ማሳደጊያ ግብአትና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአኩሪ አተርን አማካይ ምርታማነት በሄክታር ወደ 28 ኩንታል፤ ሰሊጥን ደግሞ ወደ ዘጠኝ ኩንታል ለማሳደግ ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው።

በአሁኑ ወቅት ያለው የዝናብ ስርጭት ለዘር ሥራና ለሰብል ልማቱ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ በመኸር እርሻ ለኢንዱስትሪዎች ግብአት እና ለውጪ ንግድ የሚሆን በቂ ምርት ለማምረት እንደሚያስችልም ገልጸዋል።

በአኩሪ አተርና ሰሊጥ ከሚለማው ሰብል ከ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ጥራቱን ጠብቆ ለማምረትና ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑንም ማንደፍሮ (ዶ/ር) ተናግረዋል።


በምዕራብ ጎንደር ዞን በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩት ባለሃብት አቶ ሃብቱ ጽዱ በበኩላቸው እንዳሉት፣ 643 ሄክታር መሬት ገበያ ተኮር በሆኑ ሰብሎች በመሸፈን እያለሙ ይገኛሉ።በዚህም ሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ ሱፍ እና ጥጥ እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የዘር ሥራቸውን አጠናቀው ወደ አረምና እንክብካቤ ሥራ መግባታቸውንና ከልማቱም የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።

በዘንድሮ የመኸር ወቅት ከአምስት ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥና አኩሪ አተር ሰብል ማልማታቸውን የገለጹት ደግሞ በዞኑ የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ አርሶ አደር ታደሰ አይናለም ናቸው።

የዝናብ ሥርጭቱ ለሰብል ልማቱ አመቺ ሁኔታን በመፍጠሩ የተሻለ ምርት አገኛለሁ ብለው እንዲጠብቁ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በ2016/2017 የምርት ዘመን በክልሉ በሰሊጥና በአኩሪ አተር ሰብል ከለማው መሬት 10 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ተሰብስቦ ለገበያ ቀርቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026