የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለውጭ ገበያ ለሚቀርቡ ሰሊጥና አኩሪ አተር ልማት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

Jul 25, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦በአማራ ክልል ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ለውጭ ገበያ ለሚቀርቡ የሰሊጥና አኩሪ አተር ልማት ልዩ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

በክልሉ የክረምት መግባትን ተከትሎ በተሰራው ሥራ እስካሁን 500 ሺህ ሄክታር መሬት በሰሊጥና በአኩሪ አተር ሰብሎች በዘር መሸፈኑ ተመልክቷል።


በቢሮው የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር ማንደፍሮ አስላከ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፣ በክልሉ ለኢንዱስትሪ ግብአትና ለወጪ ንግድ የሚሆኑ ሰብሎችን ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው።

በዚህም በ2017/18 የምርት ዘመን 781 ሺህ ሄክታር መሬት በአኩሪ አተርና ሰሊጥ ሰብሎች ለመሸፈን ታቅዶ በተሰራው ስራ እስካሁን ድረስ 500 ሺህ ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ተችሏል ብለዋል።

ከዕቅዱ ጋር ሲነጻጸርም ያልታረሰ ቀሪ መሬት እንዳለ ገልጸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁሉንም መሬት በመዝራት ወደ አረምና እንክብካቤ ሥራ ለመግባት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ የምርት ማሳደጊያ ግብአትና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የአኩሪ አተርን አማካይ ምርታማነት በሄክታር ወደ 28 ኩንታል፤ ሰሊጥን ደግሞ ወደ ዘጠኝ ኩንታል ለማሳደግ ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው።

በአሁኑ ወቅት ያለው የዝናብ ስርጭት ለዘር ሥራና ለሰብል ልማቱ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ በመኸር እርሻ ለኢንዱስትሪዎች ግብአት እና ለውጪ ንግድ የሚሆን በቂ ምርት ለማምረት እንደሚያስችልም ገልጸዋል።

በአኩሪ አተርና ሰሊጥ ከሚለማው ሰብል ከ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ጥራቱን ጠብቆ ለማምረትና ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑንም ማንደፍሮ (ዶ/ር) ተናግረዋል።


በምዕራብ ጎንደር ዞን በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩት ባለሃብት አቶ ሃብቱ ጽዱ በበኩላቸው እንዳሉት፣ 643 ሄክታር መሬት ገበያ ተኮር በሆኑ ሰብሎች በመሸፈን እያለሙ ይገኛሉ።በዚህም ሰሊጥ፣ አኩሪ አተር፣ ሱፍ እና ጥጥ እያለሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት የዘር ሥራቸውን አጠናቀው ወደ አረምና እንክብካቤ ሥራ መግባታቸውንና ከልማቱም የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸዋል።

በዘንድሮ የመኸር ወቅት ከአምስት ሄክታር በላይ መሬት በሰሊጥና አኩሪ አተር ሰብል ማልማታቸውን የገለጹት ደግሞ በዞኑ የምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ አርሶ አደር ታደሰ አይናለም ናቸው።

የዝናብ ሥርጭቱ ለሰብል ልማቱ አመቺ ሁኔታን በመፍጠሩ የተሻለ ምርት አገኛለሁ ብለው እንዲጠብቁ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

ከክልሉ ግብርና ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው በ2016/2017 የምርት ዘመን በክልሉ በሰሊጥና በአኩሪ አተር ሰብል ከለማው መሬት 10 ነጥብ 3 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ምርት ተሰብስቦ ለገበያ ቀርቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025