
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦በሳይንስ ሙዚየሙ ኢትዮጵያ አስደናቂ የሳይንስና የፈጠራ ጉዞ ላይ መሆኗን ተመልክቻለሁ ሲሉ የኩባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆርጌ ሉዊስ ገለጹ።
የኩባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆርጌ ሉዊስ ታፒያ ፎንሴካ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር በመሆን ሳይንስ ሙዚየምን ጎብኝተዋል።
በሙዚየሙ ቋሚ ኤግዚቢሽኑ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል፣ የግብርና፣ የውሃና ኢነርጂ እንዲሁም የኤሮስፔስ እና አቪየሽን ማሳያዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆርጌ ሉዊስ በሳይንስ ሙዚየም ኢትዮጵያ አስደናቂ የሳይንስና የፈጠራ ጉዞ ላይ መሆኗን ተመልክቻለሁ ብለዋል።

አፍሪካ የኋላቀርነት መጥፎ ትርክትን ዘመኑን በዋጀ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ተጨባጭ ሥራዎች እየቀየረች እንደምትገኝ ኢትዮጵያ ሁነኛ ማሳያ ናት ብለዋል።
ሳይንስ ሙዚየም ከኢትዮጵያ አልፎ አፍሪካ አሁን የደረሰችበትንና የመጪውን ዘመን የቴክኖሎጂ ዘመን ራዕይዋን የሚያሳይ መሆኑን መገንዘባቸውንም ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ እና ኩባ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ ጉዳዮች ዙሪያ ትብብራቸውን ለማጠናከር በጋራ ለመስራት መስማማታቸው ተገልጿል፡፡
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026