
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 21/2017(ኢዜአ)፦በሳይንስ ሙዚየሙ ኢትዮጵያ አስደናቂ የሳይንስና የፈጠራ ጉዞ ላይ መሆኗን ተመልክቻለሁ ሲሉ የኩባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆርጌ ሉዊስ ገለጹ።
የኩባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆርጌ ሉዊስ ታፒያ ፎንሴካ ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር በመሆን ሳይንስ ሙዚየምን ጎብኝተዋል።
በሙዚየሙ ቋሚ ኤግዚቢሽኑ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ የአየር ንብረት ለውጥ መከላከል፣ የግብርና፣ የውሃና ኢነርጂ እንዲሁም የኤሮስፔስ እና አቪየሽን ማሳያዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆርጌ ሉዊስ በሳይንስ ሙዚየም ኢትዮጵያ አስደናቂ የሳይንስና የፈጠራ ጉዞ ላይ መሆኗን ተመልክቻለሁ ብለዋል።

አፍሪካ የኋላቀርነት መጥፎ ትርክትን ዘመኑን በዋጀ የቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ተጨባጭ ሥራዎች እየቀየረች እንደምትገኝ ኢትዮጵያ ሁነኛ ማሳያ ናት ብለዋል።
ሳይንስ ሙዚየም ከኢትዮጵያ አልፎ አፍሪካ አሁን የደረሰችበትንና የመጪውን ዘመን የቴክኖሎጂ ዘመን ራዕይዋን የሚያሳይ መሆኑን መገንዘባቸውንም ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ እና ኩባ በቴክኖሎጂው ዘርፍ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያሳድጉ ጉዳዮች ዙሪያ ትብብራቸውን ለማጠናከር በጋራ ለመስራት መስማማታቸው ተገልጿል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025