የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በኮሜሳ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ የዲጂታል መሠረተ ልማት ለሀገር በቀል ኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ጉዳይ አድርጋ እየሰራች መሆኑን ማስገንዘብ ተችሏል

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦ በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ የዲጂታል መሠረተ ልማት ለሀገር በቀል ኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ጉዳይ አድርጋ እየሰራች መሆኑን ማስገንዘብ እንደቻለች የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ።

24ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ(ኮሜሳ) የመሪዎች ጉባኤ ትናንት በኬንያ ናይሮቢ ተካሂዷል።


በጉባኤው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን ጨምሮ ከኮሜሳ አባል ሀገራት የተውጣጡ የሀገራት መሪዎች ተሳትፈዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጉባኤው ባደረጉት ንግግር ዲጂታላይዜሽን የኢትዮጵያ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ወሳኝ ምሰሶ መሆኑን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደ የኮደርስ ስልጠና ኢኒሼቲቭ ባሉ ጠንካራ የዲጂታል መሠረተ ልማት በመገንባትና ሰፊ ክህሎት ከማፍራት አኳያ ኢትዮጵያ አመርቂ ውጤቶችን በማስመዝገብ ላይ እንደምትገኝ መጥቅሳቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ተናግረዋል፡፡

እነዚህ ዘርፈ ብዙ ጥረቶች የኢትዮጵያን ዕድገትና ለውጥ ለመምራት ብሎም ጠንካራ ዲጂታል መሠረተ ልማት ለመፍጠር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳዩ መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብሔራዊ መታወቂያ ሥርዓትና የመንግሥት አገልግሎቶችን አውቶሜት የማድረግ ተግባራት ለዲጂታል ዘርፉ እድገት እንደ ቁልፍ ምሳሌዎች የሚወሰዱ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

እንደ ኮደርስ ስልጠና ኢኒሼቲቭ ያሉ መርሐ ግብሮች ወጣቶች የዲጂታል ክህሎትን በመታጠቅ እና በዘርፉ ትርጉም ያለው ለውጥ እንዲያመጡ የሚያስችሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው የሀገር ውስጥ የዲጂታላይዜሽን ጥረቶች ከፍተኛ ውጤት እንዲያስገኙ ከቀጣናዊ ግቦች ጋር መጣጣም እንደሚገባም መናገራቸውን ኃላፊዋ ገልጸዋል፡፡

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም አክለውም፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ወጣቶች ለአህጉሪቱ ልማትና ዕድገት ወሳኝ ሃብት መሆናቸውን ማንሳታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ሀገራት የአህጉሪቱን የጎለበተ የወጣቶች ተሰጥኦ እና አቅም መጠቀም እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025