🔇Unmute
ቡታጅራ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ።
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሙስጠፋ ሀሰን፤ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታበዞኑ ያለውን እምቅ ሃብት በማልማት የከተማና ገጠሩን አካባቢ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው በተያዘው ዓመትም በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
በዞኑ ሰላምን በማፅናት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት ወደ አምራችነትና በዘላቂነት ራስን የመቻል ጥረት ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑንም ገልጸዋል።

በዚህም የበጋ የመስኖ ልማትን ጭምር በማጠናከር የማምረት እንዲሁም በከተሞች የኮሪደር ልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወኑ መሆናቸውን አንስተዋል።
ከኮሪደር ልማት በተጨማሪ የህዝብን ጥያቄዎች መሰረት ያደረጉና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።

የህዝብን የልማት ጥያቄዎች መሰረት ያደረጉና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች በስፋት እየተሰሩ መሆኑንም አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

ከቡታጅራ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወጣት እያሱ ታምራት እና አቶ ጌትነት ወረደ፤ የከተማዋ የኮሪደር ልማት ለዘመናዊ የከተማ እድገት መሰረት እየጣለ እና ለብዙዎችም የሥራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026