🔇Unmute
ቡታጅራ ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- የኮሪደር ልማትን ጨምሮ የህዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የምስራቅ ጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ።
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ሙስጠፋ ሀሰን፤ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታበዞኑ ያለውን እምቅ ሃብት በማልማት የከተማና ገጠሩን አካባቢ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አንስተው በተያዘው ዓመትም በተጠናከረ መልኩ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
በዞኑ ሰላምን በማፅናት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት ወደ አምራችነትና በዘላቂነት ራስን የመቻል ጥረት ልዩ ትኩረት የተሰጠው መሆኑንም ገልጸዋል።

በዚህም የበጋ የመስኖ ልማትን ጭምር በማጠናከር የማምረት እንዲሁም በከተሞች የኮሪደር ልማት ስራዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወኑ መሆናቸውን አንስተዋል።
ከኮሪደር ልማት በተጨማሪ የህዝብን ጥያቄዎች መሰረት ያደረጉና ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የተለያዩ የልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።

የህዝብን የልማት ጥያቄዎች መሰረት ያደረጉና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጡ የልማት ሥራዎች በስፋት እየተሰሩ መሆኑንም አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

ከቡታጅራ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ወጣት እያሱ ታምራት እና አቶ ጌትነት ወረደ፤ የከተማዋ የኮሪደር ልማት ለዘመናዊ የከተማ እድገት መሰረት እየጣለ እና ለብዙዎችም የሥራ እድል እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025