የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው - አቶ አብርሃም ማርሻሎ

Oct 14, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ጥቅምት 3/2018(ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጠናከር የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለፁ።

የክልሉ የሥራና ክህሎት ቢሮ ባካሄደው የሴክተር ጉባኤ አቶ አብርሃም እንደገለጹት በክልሉ ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራን በማጎልበት የዜጎች ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤታማ ተግባራት እየተከናወኑ ነው።


‎በዚህም በተለይ ወጣቶች ተወዳዳሪ በመሆንና የተሻለ ሀብት በመፍጠር ረገድ ውጤት እያስመዘገቡ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

‎የአካባቢን የልማት አቅም በመለየትና ወጣቶችን በቂ ክህሎት በማስጨበጥ እሴት በሚጨምሩ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው ተጠቃሚ የሚሆኑበት መደላድል የመፍጠር ሥራው በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

በጉባኤው የተገኙት ሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በበኩላቸው እንዳሉት እንደ ሀገር ብቁ የሰው ኃይል በማፍራትና ዘላቂና አስተማማኝ የሥራ ዕድል በመፍጠር ሀገራዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።


ክህሎት መር በሆነ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ በአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይ እንዲሁም በተቋም ግንባታ ላይ የሪፎርም አጀንዳዎችን በመቅረጽ የተለያዩ ሥራዎች እተከናወኑ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

በዚህም ላለፉት ተከታታይ አራት ዓመታት በአማካይ በዓመት 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር እንደተቻለ ጠቅሰው፣ በቀጣይም ይህን ለማጠናከር ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።

በሲዳማ ክልል ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት የሚበረታታ መሆኑን ጠቅሰው የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሚኒስቴሩ አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

የሲዳማ ክልል ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀገረፅዮን አበበ ከ2015 ዓ.ም በፊት የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራው ክህሎትን ዋንኛ ትኩረት ያደረገ ባለመሆኑ በዘርፉ የሚፈለገው ውጤት ሳይመዘገብ ቆይቷል።


ባለፉት ሁለት ዓመታት አንድም ዜጋ ያለ በቂ ክህሎትና ሥልጠና ወደሥራ እንዳይገባ አቅጣጫ ተቀምጦ ሲሰራ መቆየቱንም አመልክተዋል፡፡

ይህም ቀደም ሲል የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎች ላይ ይስተዋል የነበረው የውጤት ማጣት፣ የመበተን፣ የመሰላቸት እና ሀብት መፍጠር ያለመቻል ችግር ተፈትቶ ውጤት መታየት መጀመሩን ገልጸዋል።

እንደ ቢሮ ኃላፊዋ ገለፃ በ2017 በጀት ዓመት በመደበኛ ሥልጠና ከ30 ሺህ በላይ እንዲሁም በአጫጭርና ገበያ ተኮር ሥልጠናዎች ከ61 ሺህ በላይ ዜጎችን ማሰልጠን ተችሏል ፡፡

በሥልጠና ተቋማት፣ በአገልግሎት መስጫ እና በሥራ ማዕከላት ላይ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ሥርዐትን በመዘርጋትም ዘርፉን የማዘመን ሥራም ትኩረት መሰጠቱን አመልክተዋል።

በመድረኩ በተያዘው ዓመት በዘርፉ በሚከናወኑ ተግባራት ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን ባለፈው በጀት ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተቋማትና አጋር አካላት የዕውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025