🔇Unmute
ሆሳዕና ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦መንግስትለግብርናው ዘርፍ በሰጠው ትኩረትና ድጋፍ በምርታማነት ከተረጂነት ለመውጣት እየሰሩ መሆኑን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሞዴል አርሶ አደሮች ተናገሩ፡፡
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ያለፈውን ዓመት አፈጻጸምና የበጀት ዓመቱን የበጋ ወቅት ስራ የሚገመግም መድረክ አካሄዷል።
በመድረኩም በግብርናው ዘርፍ የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ አርሶ አደሮች ሽልማትና የዕውቅና መርሃ ግብር ተካሄዷል።
ከተሸላሚዎቹ መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው ሞደል አርሶ አደሮች በግብርናው ዘርፍ በመንግስት በተሰጠው ትኩረትና ድጋፍ በምርታማነት ከተረጂነት ለመውጣት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አርሶ አደሮቹ የሌማት ትሩፋትን ጨምሮ በተቀናጀ የግብርና ልማት ስራ ውጤታማና ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተው የተሰጣቸው እውቅና እና ሽልማትም ለተሻለ ስራ የሚያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረዋል።

ከከምባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ ሀሚዶ ጎፎሮ ቀበሌ ነዋሪው ሞዴል አርሶ አደር አብነት ዴላሞ የሌማት ትሩፋትን ጨምሮ በተቀናጀ ግብርና ስራ ላይ ተሰማርተው ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡
በተቀናጀ የግብርና አሰራር ላይ ያላቸውን ልምድ ለሌሎች አርሶ አደሮች እያካፈሉ መሆኑን ገልፀው በክልሉ መንግስት የተሰጣቸው እውቅና ለተሻለ ስራ እንዲነሳሱ እንደሚያደርጋቸው ተናግረዋል።
የግብርና ባለሙያዎችን ሙያዊ ድጋፍ በትኩረት በመከታተልና ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ አቦኮ ቀበሌ ነዋሪው ሞዴል አርሶ አደር ገብሩ ታፈሰ ናቸው።
በቆሎን በክላስተር ከማምረት ጀምሮ የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን መስኖን በመጠቀም በዓመት ሶስት ጊዜ እንደሚያመርቱም ተናግረዋል፡፡

በስልጤ ዞን አሊቾ ውሪሮ ወረዳ ሽልማት ቀበሌ ነዋሪ ሞዴል አርሶ አደር ፈዲላ ጀማል በበኩላቸው በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በቅመማ ቅመምና በእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶች ላይ በትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በጥቂት መሬት ላይ የሚያመርቱትን የሮዝመሪ ምርት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት የበለጠ የሚያነሳሳና አርሶ አደሩ የልፋቱን ዋጋ እንዲያገኝ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የቢሮው የ2018 የበጋ ወቅት የተቀናጀ የግብርና ልማት ሥራዎች የንቅናቄ መድረክ የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ሞዴል አርሶ አደሮች በተገኙበት በዱራሜ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025