የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በምርታማነት ከተረጂነት ለመውጣት እየሰራን ነው-አርሶ አደሮች 

Oct 15, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና ፤ ጥቅምት 4/2018(ኢዜአ)፦መንግስትለግብርናው ዘርፍ በሰጠው ትኩረትና ድጋፍ በምርታማነት ከተረጂነት ለመውጣት እየሰሩ መሆኑን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሞዴል አርሶ አደሮች ተናገሩ፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ያለፈውን ዓመት አፈጻጸምና የበጀት ዓመቱን የበጋ ወቅት ስራ የሚገመግም መድረክ አካሄዷል።

በመድረኩም በግብርናው ዘርፍ የተሻለ አፈፃፀም ላስመዘገቡ አርሶ አደሮች ሽልማትና የዕውቅና መርሃ ግብር ተካሄዷል።

ከተሸላሚዎቹ መካከል ኢዜአ ያነጋገራቸው ሞደል አርሶ አደሮች በግብርናው ዘርፍ በመንግስት በተሰጠው ትኩረትና ድጋፍ በምርታማነት ከተረጂነት ለመውጣት እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

አርሶ አደሮቹ የሌማት ትሩፋትን ጨምሮ በተቀናጀ የግብርና ልማት ስራ ውጤታማና ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተው የተሰጣቸው እውቅና እና ሽልማትም ለተሻለ ስራ የሚያነሳሳቸው መሆኑን ተናግረዋል።


ከከምባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ ሀሚዶ ጎፎሮ ቀበሌ ነዋሪው ሞዴል አርሶ አደር አብነት ዴላሞ የሌማት ትሩፋትን ጨምሮ በተቀናጀ ግብርና ስራ ላይ ተሰማርተው ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡

በተቀናጀ የግብርና አሰራር ላይ ያላቸውን ልምድ ለሌሎች አርሶ አደሮች እያካፈሉ መሆኑን ገልፀው በክልሉ መንግስት የተሰጣቸው እውቅና ለተሻለ ስራ እንዲነሳሱ እንደሚያደርጋቸው ተናግረዋል።

የግብርና ባለሙያዎችን ሙያዊ ድጋፍ በትኩረት በመከታተልና ተግባራዊ በማድረግ ውጤታማ መሆናቸውን የገለፁት ደግሞ በጉራጌ ዞን የአበሽጌ ወረዳ አቦኮ ቀበሌ ነዋሪው ሞዴል አርሶ አደር ገብሩ ታፈሰ ናቸው።

በቆሎን በክላስተር ከማምረት ጀምሮ የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን መስኖን በመጠቀም በዓመት ሶስት ጊዜ እንደሚያመርቱም ተናግረዋል፡፡


በስልጤ ዞን አሊቾ ውሪሮ ወረዳ ሽልማት ቀበሌ ነዋሪ ሞዴል አርሶ አደር ፈዲላ ጀማል በበኩላቸው በአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በቅመማ ቅመምና በእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶች ላይ በትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በተለይም በጥቂት መሬት ላይ የሚያመርቱትን የሮዝመሪ ምርት ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው መንግስት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት የበለጠ የሚያነሳሳና አርሶ አደሩ የልፋቱን ዋጋ እንዲያገኝ እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የቢሮው የ2018 የበጋ ወቅት የተቀናጀ የግብርና ልማት ሥራዎች የንቅናቄ መድረክ የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ሞዴል አርሶ አደሮች በተገኙበት በዱራሜ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025