የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለኢንቨስትመንትና ለንግድ ይበልጥ ምቹ ምህዳር ፈጥሯል

Oct 17, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 6/2018(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ተግባራዊ ያደረገችው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለኢንቨስትመንትና ለንግድ ይበልጥ ምቹ ምህዳር መፍጠሩን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ።

5ኛው የፓኪስታን-አፍሪካ የንግድ ልማት ጉባኤና አውደ ርዕይ መክፈቻ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ተካሂዷል።

በንግድ ልማት ጉባኤውና አውደ ርዕዩ ላይ ከ150 በላይ የፓኪስታን አምራች ድርጅቶች እየተሳተፉ መሆናቸው ተጠቁሟል።


በመክፈቻው መርሐ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የአፍሪካ መግቢያ በር መሆኗን ጠቅሰው፣ በሀገሪቱ ምቹ የኢንቨስትመንትና የንግድ ምህዳር መኖሩን አስገንዝበዋል።

መንግሥት ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ መሆኑንም አመልክተዋል።

ሚኒስትሩ አክለውም፣ በኢትዮጵያ ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች መኖራቸውን በማንሳት፣ በግብርና፣ በአምራች ኢንዱስትሪና ሌሎችም ዘርፎች ሰፊ አቅም እንዳለ ነው የጠቀሱት።

ኢትዮጵያን ጠንካራ የንግድ ማዕከል ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑንና የኢኮኖሚ ልማት ዕድገቷን የሚያስቀጥሉ በርካታ ሜጋ ፕሮጀክቶችን እየገነባች መሆኗን ተናግረዋል።


ከእነዚህም መካከል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ የግብርና ስራዎች፣ የአረንጓዴ አሻራ ተነሳሽነት፣ የተፈጥሮ ጋዝ ፕሮጀክቶች፣ የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራው ፓኪስታንን ጨምሮ ከሌሎች የዓለም ሀገራት በርካታ ባለሀብቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ኢንቨስት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረ ጠቁመዋል።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አብዱልሃኪም ሙሉ(ዶ/ር)፤ ጉባኤው የንግድ ተግዳሮቶችን በመፍታት ብሎም አዳዲስ የንግድና ኢንቨስትመንት መስኮችን ለመፍጠር እንደሚረዳ ተናግረዋል፡፡

በቀጣይ በንግድና ሌሎች አንኳር ስራዎች የተለያዩ ትብብሮችን ለማድረግ እንደሚረዳ ጠቁመው ኢትዮጵያ በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያው በርካታ ዘርፎችን ይበልጥ ምቹ እንዲሆኑ ማስቻሏን ጠቁመዋል፡፡


በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር አቲፍ ሸሪፍ በበኩላቸው፣ የንግድ ልማት ጉባኤው በፓኪስታን እና በአፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን የኢኮኖሚ አጋርነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።

በጉባኤውና በተዘጋጀው አውደ ርዕይ ከ150 በላይ የፓኪስታን ኩባንያዎች መሣተፋቸውን ጠቅሰው፣ ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሦስት ቀናት የሚካሄድ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

በአውደ ርዕዩ የሕክምና መድኃኒት ምርትና መሣሪያዎች፣ የውበትና የቆዳ እንክብካቤ ውጤቶች፣ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ምርቶች፣ የምግብና የምግብ ነክ የግብርና ምርቶች፣ የአውቶሞቲቭ መለዋወጫና ሌሎችም ምርቶች ቀርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026