የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የሚያስቆጭ ነው

Oct 27, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዶላ፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የሚያስቆጭ መሆኑን መምህራን ገለጹ፡፡

ለዘመናት የራሷ የባህር በር የነበራት ኢትዮጵያ ከባህር በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኝ ቢሆንም ከተወሰኑ ጊዜያት ወዲህ የባህር በሯን አጥታ የተቆለፈባት ሀገር ሆናለች።

የኢትዮጵያ መንግስት የባህር በር ማግኘት የህልውና ጉዳይ መሆኑን በጽኑ በማመንና ጠንካራ አቋም በመያዝ በዲፕሎማሲው ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑም የሚታወቅ ነው።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዶላ መምህራን ኮሌጅ መምህራን፥ ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የሚያስቆጭ መሆኑን አንስተዋል።

ለዘመናት የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ የሆነውን የባህር በር ለማግኘት ሁሉም ዜጋ ሊረባረብ እንደሚገባ ነው መምህራኑ የሚገልጹት።

የኮሌጁ የሰው ሀብት አቅም ግንባታ አስተዳደር ዲን ክብረወርቅ አለማየሁ፥ የባሀር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ እንጂ የቅንጦት ጥያቄ አይደለም ብለዋል፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ኢትዮጵያዊያን ተባብረን እንደጨረስነው ሁሉ የባህር በርን ለማግኘት መንግስት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የሚያደርገውን ጥረት ሁሉም ዜጋ ሊደግፍ ይገባል ብለዋል፡፡

መንግስት በድርድር፣በውይይትና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤት ለማድረግ እየሄደበት ያለው ርቀት የሚያስመሰግነው እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

የአንድ ሀገር ሰላምና ልማት ለሁሉም ጎሮቤት ሀገራት የሚተርፍ በመሆኑ ሌሎች ሀገራት የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎትና መሰረታዊ ጥያቄዎች ሊቀበሉ ይገባል ብለዋል።

በኮሌጁ የእቅድና ትምህርት አስተዳደር መምህር ወንድሙ አስፋው፥ ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት መብቷን እውን ለማድረግ በምታደርገው እንቅስቃሴ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩት ዜጎቿ ሁሉ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድምጽ ማሰማት አለባቸው ብለዋል፡፡

የባህር በር ማግኘት ለሰላም፣ልማትና እድገት ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አክለዋል፡፡

በዲፕሎማሲ ጫና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ በማሳመን የባህር በር እንድታገኝ ሁላችንም ለሀገራችን ድምጽና አምባሳደር መሆን አለብን ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በኮሌጁ የትምህርትና ዕቅድ አስተዳደር መምህር ሌሊሳ ኤቢሳ በበኩላቸው፥ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተጀመረው የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ከፍታ በባህር በር ይደገማል ብለዋል፡፡

ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ የባህር በር ባለመኖሩ ኢትዮጵያ ቀላል የማይባል ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን ማስተናገዷን አንስተዋል።

የባህር በር ጥያቄውን በድርድርና በውይይት ለመፍታት መንግስት የጀመራቸው ተግባራት እውን እንዲሆኑም የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

የሕዳሴው ግድብ ግንባታ በህዝብ ተሳትፎ እውን እንደሆነው ሁሉ ትውልዱ የባህር በር ለማግኘትም የተባበረ ክንዱን በማሳየት ሌላ ታሪክ እንደሚሰራም ተስፋቸውን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026