የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የሚያስቆጭ ነው

Oct 27, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዶላ፤ጥቅምት 16/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የሚያስቆጭ መሆኑን መምህራን ገለጹ፡፡

ለዘመናት የራሷ የባህር በር የነበራት ኢትዮጵያ ከባህር በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኝ ቢሆንም ከተወሰኑ ጊዜያት ወዲህ የባህር በሯን አጥታ የተቆለፈባት ሀገር ሆናለች።

የኢትዮጵያ መንግስት የባህር በር ማግኘት የህልውና ጉዳይ መሆኑን በጽኑ በማመንና ጠንካራ አቋም በመያዝ በዲፕሎማሲው ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑም የሚታወቅ ነው።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዶላ መምህራን ኮሌጅ መምህራን፥ ኢትዮጵያ በታሪክ አጋጣሚ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የሚያስቆጭ መሆኑን አንስተዋል።

ለዘመናት የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ የሆነውን የባህር በር ለማግኘት ሁሉም ዜጋ ሊረባረብ እንደሚገባ ነው መምህራኑ የሚገልጹት።

የኮሌጁ የሰው ሀብት አቅም ግንባታ አስተዳደር ዲን ክብረወርቅ አለማየሁ፥ የባሀር በር ጥያቄ የህልውና ጉዳይ እንጂ የቅንጦት ጥያቄ አይደለም ብለዋል፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ኢትዮጵያዊያን ተባብረን እንደጨረስነው ሁሉ የባህር በርን ለማግኘት መንግስት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የሚያደርገውን ጥረት ሁሉም ዜጋ ሊደግፍ ይገባል ብለዋል፡፡

መንግስት በድርድር፣በውይይትና በሰጥቶ መቀበል መርህ ኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤት ለማድረግ እየሄደበት ያለው ርቀት የሚያስመሰግነው እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

የአንድ ሀገር ሰላምና ልማት ለሁሉም ጎሮቤት ሀገራት የሚተርፍ በመሆኑ ሌሎች ሀገራት የኢትዮጵያን የመልማት ፍላጎትና መሰረታዊ ጥያቄዎች ሊቀበሉ ይገባል ብለዋል።

በኮሌጁ የእቅድና ትምህርት አስተዳደር መምህር ወንድሙ አስፋው፥ ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት መብቷን እውን ለማድረግ በምታደርገው እንቅስቃሴ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩት ዜጎቿ ሁሉ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድምጽ ማሰማት አለባቸው ብለዋል፡፡

የባህር በር ማግኘት ለሰላም፣ልማትና እድገት ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አክለዋል፡፡

በዲፕሎማሲ ጫና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ በማሳመን የባህር በር እንድታገኝ ሁላችንም ለሀገራችን ድምጽና አምባሳደር መሆን አለብን ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በኮሌጁ የትምህርትና ዕቅድ አስተዳደር መምህር ሌሊሳ ኤቢሳ በበኩላቸው፥ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የተጀመረው የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ከፍታ በባህር በር ይደገማል ብለዋል፡፡

ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ የባህር በር ባለመኖሩ ኢትዮጵያ ቀላል የማይባል ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን ማስተናገዷን አንስተዋል።

የባህር በር ጥያቄውን በድርድርና በውይይት ለመፍታት መንግስት የጀመራቸው ተግባራት እውን እንዲሆኑም የበኩላቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

የሕዳሴው ግድብ ግንባታ በህዝብ ተሳትፎ እውን እንደሆነው ሁሉ ትውልዱ የባህር በር ለማግኘትም የተባበረ ክንዱን በማሳየት ሌላ ታሪክ እንደሚሰራም ተስፋቸውን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026