የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኢትዮጵያ  የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ የበኩላችንን እየተወጣን ነው - የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በሰላማዊ፣ በሰጥቶ መቀበልና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል።


በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያን ቀይ ባህርን እንድታጣ ያደረገውን ውሳኔ ማን ወሰነ ብለን ስንፈልግ ተቋማት አልገቡበትም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም ብለዋል።


ኢዜአ ያነጋገራቸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፍትሃዊ፣ ምክንያታዊና የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የምክር ቤት አባል አቶ ሳዲቅ አደም እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዓለም አቀፍ የሕግ ማዕቀፍና በተለያዩ ኮንቬንሽኖች ተቀባይነት ያለው ነው ።


ኢትዮጵያ ከባህር በር ርቃ የቆየችበት መንገድ ተገቢ አለመሆኑን ጠቁመው፤ የኢትዮጵያ ጥያቄ የሰጥቶ መቀበል መርህን እና ሰላማዊ መንገድን ያስቀደመ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ስኬታማ እንዲሆን ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ አሳስበው፤ ምክር ቤቱም አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

የምክር ቤት አባል አስቴር ከፍታው በበኩላቸው፤ የባህር በር ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል፡፡


ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚ መሆን የምትፈልገው በሰላማዊ መንገድ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህ ስኬት የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ መላው ሕዝብ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በፍጥነት እያደገ በመምጣቱ የባህር በር ይህንኑ ፍላጎት ለማሳካት መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

የምክር ቤት አባል አምባሳደር ተውፊቅ አብዱላሂ (ዲ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የመላው ሕዝብ አጀንዳ መሆኑን ተናግረው፣ አጀንዳው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚነት ጥያቄ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተመሰረት መሆኑን ጠቁመው፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት አለበት ብለዋል።

ፍትሐዊ የሆነው ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ አስፈላጊውን ሁሉ በማድረግ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025