የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ  የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ የበኩላችንን እየተወጣን ነው - የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት

Oct 29, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ጥቅምት 18/2018(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በሰላማዊ፣ በሰጥቶ መቀበልና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት የጀመረችው ጥረት እንዲሳካ የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገለጹ፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት አካሂዷል።


በዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ማብራሪያ፤ የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያን ቀይ ባህርን እንድታጣ ያደረገውን ውሳኔ ማን ወሰነ ብለን ስንፈልግ ተቋማት አልገቡበትም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም ብለዋል።


ኢዜአ ያነጋገራቸው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ፍትሃዊ፣ ምክንያታዊና የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የምክር ቤት አባል አቶ ሳዲቅ አደም እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዓለም አቀፍ የሕግ ማዕቀፍና በተለያዩ ኮንቬንሽኖች ተቀባይነት ያለው ነው ።


ኢትዮጵያ ከባህር በር ርቃ የቆየችበት መንገድ ተገቢ አለመሆኑን ጠቁመው፤ የኢትዮጵያ ጥያቄ የሰጥቶ መቀበል መርህን እና ሰላማዊ መንገድን ያስቀደመ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ስኬታማ እንዲሆን ሁሉም ሊረባረብ እንደሚገባ አሳስበው፤ ምክር ቤቱም አስፈላጊውን እገዛ በማድረግ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

የምክር ቤት አባል አስቴር ከፍታው በበኩላቸው፤ የባህር በር ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ መሆኑን አንስተዋል፡፡


ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚ መሆን የምትፈልገው በሰላማዊ መንገድ መሆኑን ጠቁመው፤ ለዚህ ስኬት የምክር ቤት አባላትን ጨምሮ መላው ሕዝብ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በፍጥነት እያደገ በመምጣቱ የባህር በር ይህንኑ ፍላጎት ለማሳካት መሰረታዊ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

የምክር ቤት አባል አምባሳደር ተውፊቅ አብዱላሂ (ዲ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ የመላው ሕዝብ አጀንዳ መሆኑን ተናግረው፣ አጀንዳው በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት እያገኘ መምጣቱን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚነት ጥያቄ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተመሰረት መሆኑን ጠቁመው፤ ጥያቄው በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ማግኘት አለበት ብለዋል።

ፍትሐዊ የሆነው ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ አስፈላጊውን ሁሉ በማድረግ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025