የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ለኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት አቅም የሚሆን የሰው ሃይል እያፈራን ነው -ኢንስቲትዩቱ

Oct 31, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 20/2018(ኢዜአ)፡- ለኢትዮጵያ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ስኬት አቅም የሚሆን የሰው ሃይል እያፈራ እንደሚገኝ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ገለጸ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ማብራሪያቸው የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ወደተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ፕሮጀክቶቸ ዕውን መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያም ሀገርን ከጸጋዎቿ በማሰናሰል በብዝኅ የኢኮኖሚ ልማት ዕመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ ያስቻሉ የአሰራር ሥርዓቶች መዘርጋታቸውን አስረድተዋል።

በማዕድን ዘርፍም የተፈጥሮ ጋዝ፣ ነዳጅና ሌሎች የማዕድን ጸጋዎችን በማልማት የኢትዮጵያን ዕድገት ወደተሻለ ማዕራፍ የሚያሸጋግሩ ግዙፍ ብሔራዊ ፕሮጀክቶች መጀመራቸውን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ዕመርታ ለማስቀጠል ከዳንጎቴ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር የተጀመረው የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካም የአርሶ አደሩን የግብዓት አቅርቦት ፍላጎት እንደሚፈታ አንስተዋል።

ኢትዮጵያን የአፍሪካ የአቬየሽን ኢንዱስትሪ ማዕከል የሚያደርጋት የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ፕሮጀክትን በተቀመጠለት የግንባታ ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ብሩክ ከድር (ዶ/ር)፤ በትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ንድፈ ሃሳብን ከተግባር በማዋሐድ ዕውቀትና ክህሎት የተላበሰ የሰው ሃይል እያፈሩ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም ኢንስቲትዩቱ የሚያፈራው የሰው ሃይልም ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ ስኬታማነት አዎንታዊ ሚና እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።

ለአብነትም በታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሂደት ከ400 በላይ ብቁ የብረታ ብረት ብየዳ ሙያተኞችን አሰልጥኖ በማሰማራት ገንቢ ሚና መወጣቱን አስረድተዋል።

በቀጣይም በዕውቀትና ክህሎት መር ትምህርትና ስልጠና በተለያዩ መርሃ ግብሮች ለኢትዮጵያ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ስኬት አቅም የሚሆን የሰው ሃይል የማፍራት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

አዳዲስ ስልጠና መርሃ ግብሮችን በመቅረጽ ጭምር በግብርና ማቀነባበር፣ ሥነ-ውበት፣ በቆዳና ሌጦ ተያያዥ የኢንዱስትሪ መስኮችም ብቃት ያላቸው ሙያተኞችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝ አንስተዋል።

በፕላስቲክ ቴክኖሎጂ፣ በተሽከርካሪ ጥገና ዘርፎችም የትምህርትና ስልጠና መርሃ ግብር በመስጠት የዘርፉን ዕድገት የሚደግፍ የሰው ሃብት እንደሚያፈሩ ገልጸዋል።

በመጨረሻም በቅርቡ የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች አስፈላጊ የሆኑ ሙያተኞችን ማፍራት የኢንስቲትዩቱ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢንስቲትዩቱ በዚህ ላይ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025