የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በማእከላዊ ጎንደር ዞን በተመረጡ ቀበሌዎች የገጠር ኮሪደር ልማት ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦በማእከላዊ ጎንደር ዞን በያዝነው ዓመት በተመረጡ ቀበሌዎች በገጠር ኮሪደር ልማት የሞዴል የአርሶ አደሮች መንደርን ለመገንባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ ለኢዜአ እንደገለጹት የገጠር ኮሪደር ልማቱ አርሶ አደሩን ወደ ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ በማሸጋገር በገጠሩና በከተማ መካከል የተሳሰረ ኢኮኖሚያዊ እድገት ለመፍጠር የሚያስችል ነው።

የገጠር ኮሪደር ልማቱ በዞኑ በሚገኙ 15 ወረዳዎች በተመረጡ 15 ሞዴል የገጠር ቀበሌዎች ተግባራዊ ለማድረግ ከህብረተሰቡ ጋር መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል።

የገጠር ኮሪደር ልማቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የማስፈጸሚያ ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወጥ የሆኑ የሞዴል አርሶ አደሮች መንደሮችን ለመገንባት የሚያስችል ንድፍ እየተዘጋጀ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የገጠር ኮሪደር ልማቱ የሞዴል አርሶ አደሮች መኖሪያን ጨምሮ የትምህርት፣ የጤና፣ የግብርና፣ የመንገድ፣ የመጠጥ ውሃና አማራጭ የኢነርጂ መሰረተ ልማቶችን ባካተተ መልኩ እንደሚገነባ አስረድተዋል።

ለገጠር ኮሪደር ልማቱ የተመረጡ ቀበሌዎች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡና በተጨባጭ የአርሶ አደሩን ህይወት በመቀየር ሞዴልነታቸውን ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል፡፡

የገጠር ኮሪደር ልማቱ በገጠር የሚኖረውን ሰፊ ቁጥር ያለውን አርሶ አደር የእውቀት፣ የዘመናዊነትና የቴክኖሎጂ ተቋዳሽ ማድረግ የሚያስችል አዲስ ሃሳብና ራእይ የያዘ ነው ያሉት ደግሞ የማእከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ክንዱ ዘውዱ ናቸው፡፡


የገጠር ኮሪደር ልማቱ የገጠሩን ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጥ ጠቁመው ፍትሃዊና የተመጣጠነ የኢኮኖሚ እድገትን የሚያሰፍን በመሆኑ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል ይደረጋል ብለዋል፡፡

የላይ አርማጭሆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስረሳው ደሴ በበኩላቸው በዚህ ዓመት በወረዳው የኮሪደር ልማቱን ለማስጀመር አንድ ሞዴል የገጠር ቀበሌ መመረጡን ተናግረዋል፡፡


ለገጠር ኮሪደር ልማቱ የሚያስፈልገውን የሎጂስቲክስ፣ የባለሙያዎች፣ የበጀት ድጋፍ የማስተባበርና የማደራጀት ስራዎች መጠናቀቁን ጠቁመው የሞዴል አርሶ አደሮች መንደር ቅየሳ አሁን ላይ መጀመሩንም አስረድተዋል፡፡

የገጠር ኮሪደር ልማቱ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ በመቀየር ሀገሪቱ ወደ ብዝሃ ኢኮኖሚ ሽግግር ለማድረግ የጀመረችውን መዋቅራዊ የኢኮኖሚ እድገት የሚያፋጥን መሆኑንም አመልክተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025