የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በማእከላዊ ጎንደር ዞን በተመረጡ ቀበሌዎች የገጠር ኮሪደር ልማት ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ ጥቅምት 29/2018(ኢዜአ)፦በማእከላዊ ጎንደር ዞን በያዝነው ዓመት በተመረጡ ቀበሌዎች በገጠር ኮሪደር ልማት የሞዴል የአርሶ አደሮች መንደርን ለመገንባት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ፡፡

የመምሪያው ኃላፊ አቶ ንጉሴ ማለደ ለኢዜአ እንደገለጹት የገጠር ኮሪደር ልማቱ አርሶ አደሩን ወደ ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ በማሸጋገር በገጠሩና በከተማ መካከል የተሳሰረ ኢኮኖሚያዊ እድገት ለመፍጠር የሚያስችል ነው።

የገጠር ኮሪደር ልማቱ በዞኑ በሚገኙ 15 ወረዳዎች በተመረጡ 15 ሞዴል የገጠር ቀበሌዎች ተግባራዊ ለማድረግ ከህብረተሰቡ ጋር መግባባት ላይ መደረሱን ገልጸዋል።

የገጠር ኮሪደር ልማቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የማስፈጸሚያ ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወጥ የሆኑ የሞዴል አርሶ አደሮች መንደሮችን ለመገንባት የሚያስችል ንድፍ እየተዘጋጀ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የገጠር ኮሪደር ልማቱ የሞዴል አርሶ አደሮች መኖሪያን ጨምሮ የትምህርት፣ የጤና፣ የግብርና፣ የመንገድ፣ የመጠጥ ውሃና አማራጭ የኢነርጂ መሰረተ ልማቶችን ባካተተ መልኩ እንደሚገነባ አስረድተዋል።

ለገጠር ኮሪደር ልማቱ የተመረጡ ቀበሌዎች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡና በተጨባጭ የአርሶ አደሩን ህይወት በመቀየር ሞዴልነታቸውን ያረጋገጡ ናቸው ብለዋል፡፡

የገጠር ኮሪደር ልማቱ በገጠር የሚኖረውን ሰፊ ቁጥር ያለውን አርሶ አደር የእውቀት፣ የዘመናዊነትና የቴክኖሎጂ ተቋዳሽ ማድረግ የሚያስችል አዲስ ሃሳብና ራእይ የያዘ ነው ያሉት ደግሞ የማእከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ ክንዱ ዘውዱ ናቸው፡፡


የገጠር ኮሪደር ልማቱ የገጠሩን ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጥ ጠቁመው ፍትሃዊና የተመጣጠነ የኢኮኖሚ እድገትን የሚያሰፍን በመሆኑ ተገቢውን ድጋፍና ክትትል ይደረጋል ብለዋል፡፡

የላይ አርማጭሆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አስረሳው ደሴ በበኩላቸው በዚህ ዓመት በወረዳው የኮሪደር ልማቱን ለማስጀመር አንድ ሞዴል የገጠር ቀበሌ መመረጡን ተናግረዋል፡፡


ለገጠር ኮሪደር ልማቱ የሚያስፈልገውን የሎጂስቲክስ፣ የባለሙያዎች፣ የበጀት ድጋፍ የማስተባበርና የማደራጀት ስራዎች መጠናቀቁን ጠቁመው የሞዴል አርሶ አደሮች መንደር ቅየሳ አሁን ላይ መጀመሩንም አስረድተዋል፡፡

የገጠር ኮሪደር ልማቱ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ በመቀየር ሀገሪቱ ወደ ብዝሃ ኢኮኖሚ ሽግግር ለማድረግ የጀመረችውን መዋቅራዊ የኢኮኖሚ እድገት የሚያፋጥን መሆኑንም አመልክተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025