🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2018(ኢዜአ)፦ የብራውን ፉድ ፋብሪካ የአርሶ አደሮችን የግብርና ምርታማነት በመጨምር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እንደሚያሳድግ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ከተማ የተገነባውን የብራውን ፉድ የበቆሎ፣ ብቅልና አልሚ ምግብ ማምረቻ ፋብሪካን መርቀው ከፍተዋል።
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የብራውን ፉድ ፋብሪካ የግብርና ምርቶችን ውጤታማነት በማሳደግ የኢንዱስትሪ ሽግግርን የሚያሳልጥ ነው።
የበለጸገ የምግብ አቅርቦትን በማሻሻል በአዕምሮና የአካል ዕድገት ጥራት ያለው ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል።
በሁሉም የኢንዱስትሪ የልማት አቅጣጫዎች የተነደፉ ትልሞችን አሰናስሎ የያዘ ፋብሪካ መሆኑንም ገልጸዋል።
በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስክም ፍትሕዊ የመሰረተ ልማት ሥርጭትን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ መሆኑን አንስተዋል።
የበቆሎ ምርትን በግብዓትነት የሚጠቀመው ፋብሪካው አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።
በስራ ዕድል ፈጠራና ፍትሃዊ የኢንቨስትመንት ሥርጭትን በማስፋት ለዘላቂ የኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሠረት መሆኑን አንስተዋል።
ፋብሪካው የሚጠቀመው ግብዓትም በእሴት ሰንሰለት የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጥ አስረድተዋል።
የክልሉን አምራች ኢንዱስትሪ ተጠቃሚነት በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ የምግብ ምርቶችን በመተካት አይነተኛ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል።
የአማራ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ በግብርና እና ሌሎች መስኮች የመልማት ዕምቅ አቅም እንዳለው በተግባርም ሆነ በጥናት መረጋገጡን አውስተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025