የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የብራውን ፉድ ፋብሪካ የአርሶ አደሮችን የግብርና ምርታማነት በመጨምር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ያሳድጋል - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ 

Nov 13, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ህዳር 2/2018(ኢዜአ)፦ የብራውን ፉድ ፋብሪካ የአርሶ አደሮችን የግብርና ምርታማነት በመጨምር የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን እንደሚያሳድግ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ከተማ የተገነባውን የብራውን ፉድ የበቆሎ፣ ብቅልና አልሚ ምግብ ማምረቻ ፋብሪካን መርቀው ከፍተዋል።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የብራውን ፉድ ፋብሪካ የግብርና ምርቶችን ውጤታማነት በማሳደግ የኢንዱስትሪ ሽግግርን የሚያሳልጥ ነው።

የበለጸገ የምግብ አቅርቦትን በማሻሻል በአዕምሮና የአካል ዕድገት ጥራት ያለው ማህበረሰብ ለመገንባት ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል።

በሁሉም የኢንዱስትሪ የልማት አቅጣጫዎች የተነደፉ ትልሞችን አሰናስሎ የያዘ ፋብሪካ መሆኑንም ገልጸዋል።

በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስክም ፍትሕዊ የመሰረተ ልማት ሥርጭትን በማስፋት የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ መሆኑን አንስተዋል።

የበቆሎ ምርትን በግብዓትነት የሚጠቀመው ፋብሪካው አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ የሀገርን ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።

በስራ ዕድል ፈጠራና ፍትሃዊ የኢንቨስትመንት ሥርጭትን በማስፋት ለዘላቂ የኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ መሠረት መሆኑን አንስተዋል።

ፋብሪካው የሚጠቀመው ግብዓትም በእሴት ሰንሰለት የአርሶ አደሩን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጥ አስረድተዋል።

የክልሉን አምራች ኢንዱስትሪ ተጠቃሚነት በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ የምግብ ምርቶችን በመተካት አይነተኛ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል።

የአማራ ክልል በአምራች ኢንዱስትሪ፣ ማዕድን፣ በግብርና እና ሌሎች መስኮች የመልማት ዕምቅ አቅም እንዳለው በተግባርም ሆነ በጥናት መረጋገጡን አውስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026