🔇Unmute
ሰቆጣ ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡- የመስኖ ልማት አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ምርታማነትን የማሳደግና ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማትና ብዝሃ መር የኢኮኖሚ ልማትን በመከተል ከተረጅነት ወደ አምራችነት የመሸጋገር ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በተለይም ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት የምርት አማራጮችን የማስፋትና ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጎ በመሰራት ላይ ይገኛል።

የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ የመስኖ ልማት አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ፤ የመስኖ ልማትን በማጠናከር መሬት ፆም ማደር የለበትም በሚል መርህ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል።

በአካባቢው የመስኖ ልማት አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ምርታማነትን የማሳደግና ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት በዘንድሮው የበጋ መስኖ 4 ሺህ 738 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ከግማሽ በላይ ማሳካት ስለመቻሉ አንስተዋል።
በአካባቢው በመስኖ ልማት እየተሳተፉ ያሉ አርሶ አደሮችም በባለሙያዎች ድጋፍና የግብአት አቅርቦት በመታገዝ የተሻለ ምርት ለማግኘት እየሰራን ነው ብለዋል።
በተለይም የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ቶሎ የሚደርሱ ሰብሎችን በመዝራት በበጋው ምርት በማግኘት ከችግር ለመውጣት የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑንም ተናግረዋል።

በብሄረሰብ አስተዳደሩ በአበርገሌ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መሰረት ወልደየስ፤ በወረዳው በ1ኛ እና ሁለተኛ ዙር የተለያዩ ሰብሎችን በመስኖ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን የልማት ስራው በስኬት መቀጠሉን ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025