🔇Unmute
ሰቆጣ ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡- የመስኖ ልማት አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ምርታማነትን የማሳደግና ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማትና ብዝሃ መር የኢኮኖሚ ልማትን በመከተል ከተረጅነት ወደ አምራችነት የመሸጋገር ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በተለይም ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት የምርት አማራጮችን የማስፋትና ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጎ በመሰራት ላይ ይገኛል።

የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ የመስኖ ልማት አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ፤ የመስኖ ልማትን በማጠናከር መሬት ፆም ማደር የለበትም በሚል መርህ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል።

በአካባቢው የመስኖ ልማት አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ምርታማነትን የማሳደግና ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት በዘንድሮው የበጋ መስኖ 4 ሺህ 738 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ከግማሽ በላይ ማሳካት ስለመቻሉ አንስተዋል።
በአካባቢው በመስኖ ልማት እየተሳተፉ ያሉ አርሶ አደሮችም በባለሙያዎች ድጋፍና የግብአት አቅርቦት በመታገዝ የተሻለ ምርት ለማግኘት እየሰራን ነው ብለዋል።
በተለይም የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ቶሎ የሚደርሱ ሰብሎችን በመዝራት በበጋው ምርት በማግኘት ከችግር ለመውጣት የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑንም ተናግረዋል።

በብሄረሰብ አስተዳደሩ በአበርገሌ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መሰረት ወልደየስ፤ በወረዳው በ1ኛ እና ሁለተኛ ዙር የተለያዩ ሰብሎችን በመስኖ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን የልማት ስራው በስኬት መቀጠሉን ገልጸዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026