የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የመስኖ ልማት አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰቆጣ ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡- የመስኖ ልማት አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ምርታማነትን የማሳደግና ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

በኢትዮጵያ ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማትና ብዝሃ መር የኢኮኖሚ ልማትን በመከተል ከተረጅነት ወደ አምራችነት የመሸጋገር ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በተለይም ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት የምርት አማራጮችን የማስፋትና ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጎ በመሰራት ላይ ይገኛል።


የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ የመስኖ ልማት አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ፤ የመስኖ ልማትን በማጠናከር መሬት ፆም ማደር የለበትም በሚል መርህ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል።


በአካባቢው የመስኖ ልማት አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ምርታማነትን የማሳደግና ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል።

በዚህም መሰረት በዘንድሮው የበጋ መስኖ 4 ሺህ 738 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ከግማሽ በላይ ማሳካት ስለመቻሉ አንስተዋል።

በአካባቢው በመስኖ ልማት እየተሳተፉ ያሉ አርሶ አደሮችም በባለሙያዎች ድጋፍና የግብአት አቅርቦት በመታገዝ የተሻለ ምርት ለማግኘት እየሰራን ነው ብለዋል።

በተለይም የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ቶሎ የሚደርሱ ሰብሎችን በመዝራት በበጋው ምርት በማግኘት ከችግር ለመውጣት የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑንም ተናግረዋል።


በብሄረሰብ አስተዳደሩ በአበርገሌ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መሰረት ወልደየስ፤ በወረዳው በ1ኛ እና ሁለተኛ ዙር የተለያዩ ሰብሎችን በመስኖ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን የልማት ስራው በስኬት መቀጠሉን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025