🔇Unmute
ሰቆጣ ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፡- የመስኖ ልማት አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ምርታማነትን የማሳደግና ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ያሉ እምቅ ሃብቶችን በማልማትና ብዝሃ መር የኢኮኖሚ ልማትን በመከተል ከተረጅነት ወደ አምራችነት የመሸጋገር ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በተለይም ለድርቅ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየት የምርት አማራጮችን የማስፋትና ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት ተደርጎ በመሰራት ላይ ይገኛል።

የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ግብርና መምሪያ የመስኖ ልማት አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ደሳለኝ አዳነ፤ የመስኖ ልማትን በማጠናከር መሬት ፆም ማደር የለበትም በሚል መርህ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል።

በአካባቢው የመስኖ ልማት አቅምን በአግባቡ በመጠቀም ምርታማነትን የማሳደግና ከተረጅነት የመውጣት ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል።
በዚህም መሰረት በዘንድሮው የበጋ መስኖ 4 ሺህ 738 ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ እስካሁን ከግማሽ በላይ ማሳካት ስለመቻሉ አንስተዋል።
በአካባቢው በመስኖ ልማት እየተሳተፉ ያሉ አርሶ አደሮችም በባለሙያዎች ድጋፍና የግብአት አቅርቦት በመታገዝ የተሻለ ምርት ለማግኘት እየሰራን ነው ብለዋል።
በተለይም የሰብል፣ የአትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም ቶሎ የሚደርሱ ሰብሎችን በመዝራት በበጋው ምርት በማግኘት ከችግር ለመውጣት የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆኑንም ተናግረዋል።

በብሄረሰብ አስተዳደሩ በአበርገሌ ወረዳ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ ወይዘሮ መሰረት ወልደየስ፤ በወረዳው በ1ኛ እና ሁለተኛ ዙር የተለያዩ ሰብሎችን በመስኖ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን የልማት ስራው በስኬት መቀጠሉን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025