የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ሕብረተሰቡን ያሳተፈ  የሰብል አሰባሰብ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፣ ሕዳር13/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን በምግብ ራስን የመቻል ፕሮግራም በሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ሰብል የማሰባሰብ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

በተጠሪ ጽሕፈት ቤቱ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ፈጣን ምላሽ ቡድን መሪ ዘላለም አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ መንግስት የችግር ጊዜ እርዳታን በራስ አቅም በመሸፈን ተረጅነትን ዜሮ ለማድረግ ርብርብ እያደረገ ነው።

ይህም በምግብ ራስን የመቻል ፕሮግራም በዞኑ ስር ከሚገኙ ወረዳዎች በሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ 110 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ የምግብ እህል ለመሰብሰብ በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል።

ተግባሩ ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመው፤ በተጨማሪም በክረምቱ ለዚሁ ዓላማ በተለያየ የሰብል ዘር ከተሸፈነው 300 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ከሰባት ሺህ 800 ኩንታል በላይ የማሽላ ምርት የሚጠበቅ መሆኑንም አመልክተዋል።


የምግብ እህል ክምችቱ ሊያጋጥሙ ለሚችሉ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።

የምግብ ሉዓዊነትን በማረጋገጥ ተረጅነትን ዜሮ ለማድረግ በመንግስት የተያዘውን ግብ ለማሳካት ዞኑ የድርሻውን ለመወጣት ርብርብ እያደረገ መሆኑ ተመላክቷል።

በመተማ ወረዳ ድጋፍ ከሚሹ ወገኖች መካከል አቶ ማለደ ቢምረው በሰጡት አስተያየት፤ በሕብረተሰቡ እና በመንግሥት ድጋፍ ላለፉት አራት ዓመታት ችግር ሳይገጥማቸው ማሳለፋቸውን ገልጸዋል።

አሁን በመተማ ወረዳ ኩመር አፍጥጥ ቀበሌ የለማው ማሽላ ለወደፊት ተስፋ እንድንሰንቅ አድርጓል ብለዋል።

በመተማ ወረዳ ኮኪት ቀበሌ አርሶአደር ደጀን አስማማው በበኩላቸው ፤ ለመጠባበቂያ ክምችት የሚጠበቅባቸውን ለማዋጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025