የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ሕብረተሰቡን ያሳተፈ  የሰብል አሰባሰብ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፣ ሕዳር13/2018(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን በምግብ ራስን የመቻል ፕሮግራም በሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ሰብል የማሰባሰብ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

በተጠሪ ጽሕፈት ቤቱ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ፈጣን ምላሽ ቡድን መሪ ዘላለም አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ መንግስት የችግር ጊዜ እርዳታን በራስ አቅም በመሸፈን ተረጅነትን ዜሮ ለማድረግ ርብርብ እያደረገ ነው።

ይህም በምግብ ራስን የመቻል ፕሮግራም በዞኑ ስር ከሚገኙ ወረዳዎች በሕብረተሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ 110 ሺህ ኩንታል የሚጠጋ የምግብ እህል ለመሰብሰብ በሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል።

ተግባሩ ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቁመው፤ በተጨማሪም በክረምቱ ለዚሁ ዓላማ በተለያየ የሰብል ዘር ከተሸፈነው 300 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ከሰባት ሺህ 800 ኩንታል በላይ የማሽላ ምርት የሚጠበቅ መሆኑንም አመልክተዋል።


የምግብ እህል ክምችቱ ሊያጋጥሙ ለሚችሉ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን አስረድተዋል።

የምግብ ሉዓዊነትን በማረጋገጥ ተረጅነትን ዜሮ ለማድረግ በመንግስት የተያዘውን ግብ ለማሳካት ዞኑ የድርሻውን ለመወጣት ርብርብ እያደረገ መሆኑ ተመላክቷል።

በመተማ ወረዳ ድጋፍ ከሚሹ ወገኖች መካከል አቶ ማለደ ቢምረው በሰጡት አስተያየት፤ በሕብረተሰቡ እና በመንግሥት ድጋፍ ላለፉት አራት ዓመታት ችግር ሳይገጥማቸው ማሳለፋቸውን ገልጸዋል።

አሁን በመተማ ወረዳ ኩመር አፍጥጥ ቀበሌ የለማው ማሽላ ለወደፊት ተስፋ እንድንሰንቅ አድርጓል ብለዋል።

በመተማ ወረዳ ኮኪት ቀበሌ አርሶአደር ደጀን አስማማው በበኩላቸው ፤ ለመጠባበቂያ ክምችት የሚጠበቅባቸውን ለማዋጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026