የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በምስራቅ ጎጃም ዞን ባለፉት አራት ወራት ከ22ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ፤ ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን በበጀት ዓመቱ ባለፉት አራት ወራት ከ22ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን የዞኑ ስራና ስልጠና መምሪያ ገለጸ።

የመምሪያው ተወካይ ሃላፊ ሙሉሰው አወቀ ለኢዜአ እንደገለጹት በዞኑ የአካባቢውን ጸጋ በጥናት በመለየት ወጣቶችን በስራ እድል ፈጠራ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው።

በበጀት ዓመቱም ከ131ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር ታቅዶ እስካሁን በተደረገ ጥረት ለ22ሺህ 267 ወጣቶች የስራ እድል መፈጠሩን ገልጸዋል።

የስራ እድሉን መፍጠር የተቻለውም በኮንስትራክሽን፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በንግድ፣ በእንጨትና ብረታብረት፣ በምግብና ምግብ ነክ እንዲሁም ሌሎች የስራ ዘርፎች መሆኑን ተናግረዋል።

ከተፈጠረው የስራ እድል ውስጥም ከ12ሺህ በላይ የሚሆኑት በቋሚ ቀሪዎቹ በጊዜያዊነት ተጠቃሚ መሆናቸው ተመልከቷል።

በኢንተርፕራይዞች የስራ እድል ለተፈጠረላቸ ወጣቶችም ከአበዳሪ ተቋማት ጋር በመተባበር ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር ማቅረብ መቻሉን አስረድተዋል።

በተጨማሪም ከ140 በላይ ሼዶችና ኮንቲነሮች እንዲሁም 17 ሄክታር መሬት ለመስሪያና መሸጫ ማተላለፉንም አስገንዝበዋል።


የስራ እድሉ ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል የአዋበል ወረዳ የሉማሜ ከተማ ነዋሪ ወጣት ኤርሚያስ መሰንበት እንዳለው ከአራት ጓደኞቹ ጋር በመደራጀት በዶሮ እርባታ የስራ ዘርፍ ተሰማርተዋል።

ካለፉት ሁለት ወራት ጀምሮ ከሶስት ሺህ በላይ እንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማስገባት እያረቡ እንደሚገኙ ጠቁመው እንቁላል መጣል ሲጀምሩ ተጠቃሚነታቸው እንደሚያድግ ተናግሯል።

የዚሁ ወረዳ የሰንበት ቀበሌ ነዋሪ ወጣት ባየልኝ ያዜ በበኩሉ አምስት ጓደኛሞች ሆነው በመደራጀት ከግማሽ ሄክታር በላይ መሬት ወስደው የጓሮ አትክልት እያለሙ እንደሚገኙ ተናግሯል።

እያለሙት ያለው የጓሮ አትክልት ጎመን፣ ቲሚቲምና ቀይ ስር አሁን ላይ ለሽያጭ በመድረሱ እስከ 80 ሺህ ብር ገቢ እንደሚጠብቁም ተናግሯል።

በዞኑ ባለፈው ዓመት ከ115 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ከመምሪያው የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025