🔇Unmute
ወላይታ ሶዶ፤ ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የደረሱ ሰብሎችን በዘመናዊ ማሽኖች ታግዞ በመሰብሰብ የምርት ብክነትን ከመከላከል ባለፈ የምርት መጠንና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።
በክልሉ በመኸር ወቅት በተለያዩ ሰብሎች ከለማው መሬት እስከ 70 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ተመላክቷል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በወላይታ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የመኸር ሰብል ያለበትን ደረጃ ተመልክተዋል፡፡
ኃላፊው በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በመኸር ወቅት ለምተው ቀድመው የደረሱ ሰብሎች ምርት መሰብሰብ ተጀምሯል፡፡

የምርት አሰባሰብ ሂደቱን በዘመናዊ ማሽኖች በማገዝ ብክነትን ከመከላከል ባለፈ የምርት መጠኑንና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።
በክልሉ በመኸር እርሻ ከለማው ከ840ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ እስከ 70 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል፡፡
በክልሉ ከ232ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በክላስተር የለማ ሲሆን፣ አርሶ አደሮችም የደረሱ ሰብሎችን በጋራ እንዲሰበስቡ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ የምርት ብክነትን በመከላከል ምርታማነትን ያሳድጋል።
ውጤታማ የሰብል ስብሰባ ሥራ ለማከናወን አርሶ አደሩንና የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት በማሳተፍ የድጋፍ ሥራ ይከናወናል ብለዋል፡፡

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሰማ በበኩላቸው ለአርሶ አደሮች ዘመናዊ የግብርና አሰራርን በማስተዋወቅ ምርትና ምርታማነትን ለማደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዚህም ከተረጂነት ለመውጣት የሚደረገውን ጥረት ከማገዝ ባለፈ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የደረሰ የመኸር ሰብልን ከብክነት በጸዳ መልኩ በኮምባይነር ታግዞ ለመሰባሰብ ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በዞኑ በመኸር የለማው ሰብል በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝና ቀድሞ የደረሰውን ከብክነት በጸዳ መልኩ የመሰባሰብ ሥራ መጀመሩን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዘማች ሶርሳ(ዶ/ር) ናቸው፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025