የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ የደረሰ ሰብልን በዘመናዊ ማሽኖች ታግዞ በመሰብሰብ የምርት ብክነትን ለመከላከል ትኩረት ተሰጥቷል

Nov 24, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ወላይታ ሶዶ፤ ህዳር 14/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የደረሱ ሰብሎችን በዘመናዊ ማሽኖች ታግዞ በመሰብሰብ የምርት ብክነትን ከመከላከል ባለፈ የምርት መጠንና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።


በክልሉ በመኸር ወቅት በተለያዩ ሰብሎች ከለማው መሬት እስከ 70 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅ ተመላክቷል።


ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በወላይታ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች የመኸር ሰብል ያለበትን ደረጃ ተመልክተዋል፡፡


ኃላፊው በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በመኸር ወቅት ለምተው ቀድመው የደረሱ ሰብሎች ምርት መሰብሰብ ተጀምሯል፡፡


የምርት አሰባሰብ ሂደቱን በዘመናዊ ማሽኖች በማገዝ ብክነትን ከመከላከል ባለፈ የምርት መጠኑንና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።


በክልሉ በመኸር እርሻ ከለማው ከ840ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ እስከ 70 ሚሊዮን ኩንታል ምርት እንደሚጠበቅም ገልጸዋል፡፡


በክልሉ ከ232ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በክላስተር የለማ ሲሆን፣ አርሶ አደሮችም የደረሱ ሰብሎችን በጋራ እንዲሰበስቡ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ የምርት ብክነትን በመከላከል ምርታማነትን ያሳድጋል።


ውጤታማ የሰብል ስብሰባ ሥራ ለማከናወን አርሶ አደሩንና የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት በማሳተፍ የድጋፍ ሥራ ይከናወናል ብለዋል፡፡


የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሳሙኤል ተሰማ በበኩላቸው ለአርሶ አደሮች ዘመናዊ የግብርና አሰራርን በማስተዋወቅ ምርትና ምርታማነትን ለማደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡


በዚህም ከተረጂነት ለመውጣት የሚደረገውን ጥረት ከማገዝ ባለፈ የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።


የደረሰ የመኸር ሰብልን ከብክነት በጸዳ መልኩ በኮምባይነር ታግዞ ለመሰባሰብ ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።


በዞኑ በመኸር የለማው ሰብል በጥሩ ቁመና ላይ እንደሚገኝና ቀድሞ የደረሰውን ከብክነት በጸዳ መልኩ የመሰባሰብ ሥራ መጀመሩን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዘማች ሶርሳ(ዶ/ር) ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025