የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የቡና ዘርፍ የላቀ ስኬት እንዲያስመዘግብ አስችሏል- ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)

Nov 26, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 16/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም የእውቅና መርኃ ግብር ተካሂዷል።


በመርኃ ግብሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ ቡና አምራቾችና ላኪዎች የተገኙ ሲሆን በቡና ወጪ ንግድ የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ላኪዎች እውቅና ተሰጥቷቸዋል።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር መንግሥት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ማድረጉ የቡና ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ አነቃቅቷል ብለዋል።


ከአራት ዓመታት ወዲህ በቡና ወጪ ንግድ እየተመዘገበ ያለው ከፍተኛ ስኬት የቡና አምራች ዜጎችን ተስፋ እያለመለመ መሆኑን ጠቅሰዋል።


በ2017 በጀት ዓመትም የተመዘገበው የቡና ወጪ ንግድ ስኬት መግሥት ከምርት እስከ ገበያ በወሰዳቸው እርምጃዎች በአርሶ አደሮችና በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ትጋት የተገኘ ስኬት ነው ብለዋል።


በቀጣይ የቡና ሜካናይዝድ እርሻን ማስፋትና ቡና ላይ እሴት ተጨምሮ መላክ የትኩረት ማዕከል መሆኑን ገልጸዋል።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የገበያ መዳረሻዎችን እያሰፋ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ቀጣይነት ያለው ፕሮሞሽንና የገበያ መዳረሻ የማስፋት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ(ዶ/ር)፥ ኢትዮጵያ ልዩ ጣዕም ያላቸው የቡና ዝርያዎች ባለቤት መሆኗን አውስተዋል።


ከለውጡ ወዲህ የኢትዮጵያ ቡና በዓለም ገበያ ተፈላጊነቱ መጨመሩን ጠቅሰው፥ በ2017 በጀት ዓመት 470 ሺህ ቶን ቡና በመላክ 2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል ብለዋል።


በዘርፉ መሠረታዊ ለውጥ በማምጣትና የቡና ምርትና ግብይት ላይ ያሉ ችግሮችን በመፍታት የተገኘ ስኬት መሆኑንም ጠቁመዋል።


ቡና የሀገር ኢኮኖሚ ዋልታነቱን እያስመሰከረ ይገኛል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፥ ጥራታቸው አስተማማኝና ተመራጭ የሆኑ የቡናና ሻይ ምርቶችን ለውጭ ገበያ የማቅረብ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026