🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 16/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት የእቅድ አፈጻጸም የእውቅና መርኃ ግብር ተካሂዷል።
በመርኃ ግብሩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ ቡና አምራቾችና ላኪዎች የተገኙ ሲሆን በቡና ወጪ ንግድ የላቀ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ላኪዎች እውቅና ተሰጥቷቸዋል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር መንግሥት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ማድረጉ የቡና ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ አነቃቅቷል ብለዋል።
ከአራት ዓመታት ወዲህ በቡና ወጪ ንግድ እየተመዘገበ ያለው ከፍተኛ ስኬት የቡና አምራች ዜጎችን ተስፋ እያለመለመ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በ2017 በጀት ዓመትም የተመዘገበው የቡና ወጪ ንግድ ስኬት መግሥት ከምርት እስከ ገበያ በወሰዳቸው እርምጃዎች በአርሶ አደሮችና በዘርፉ ባለድርሻ አካላት ትጋት የተገኘ ስኬት ነው ብለዋል።
በቀጣይ የቡና ሜካናይዝድ እርሻን ማስፋትና ቡና ላይ እሴት ተጨምሮ መላክ የትኩረት ማዕከል መሆኑን ገልጸዋል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የገበያ መዳረሻዎችን እያሰፋ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ቀጣይነት ያለው ፕሮሞሽንና የገበያ መዳረሻ የማስፋት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ(ዶ/ር)፥ ኢትዮጵያ ልዩ ጣዕም ያላቸው የቡና ዝርያዎች ባለቤት መሆኗን አውስተዋል።
ከለውጡ ወዲህ የኢትዮጵያ ቡና በዓለም ገበያ ተፈላጊነቱ መጨመሩን ጠቅሰው፥ በ2017 በጀት ዓመት 470 ሺህ ቶን ቡና በመላክ 2 ነጥብ 65 ቢሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል ብለዋል።
በዘርፉ መሠረታዊ ለውጥ በማምጣትና የቡና ምርትና ግብይት ላይ ያሉ ችግሮችን በመፍታት የተገኘ ስኬት መሆኑንም ጠቁመዋል።
ቡና የሀገር ኢኮኖሚ ዋልታነቱን እያስመሰከረ ይገኛል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፥ ጥራታቸው አስተማማኝና ተመራጭ የሆኑ የቡናና ሻይ ምርቶችን ለውጭ ገበያ የማቅረብ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025