🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 16/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የአሰላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለበጋ መስኖ እርሻ የሚውል ከአስራ አንድ ሺህ አምስት መቶ ኩንታል በላይ የስንዴ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እያሰራጨ መሆኑን ገለጸ።
ጽህፈት ቤቱ የአርሶ አደሩን የምርጥ ዘር ፍላጎት ለማሟላት በራሱ፣ በክላስተር የተደራጁ አርሶ አደሮች እና ሰፋፊ እርሻ ባላቸው ባለሃብቶች መሬት ላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን ምርጥ ዘሮች በማባዛት ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በዚህም ስንዴን ጨምሮ በበርካታ የሰብል ዓይነቶች እና ዝርያዎች መስራች፣ ቅድመ መስራች እና የተመሰከረለት የዘር ደረጃዎችን በማባዛት ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የአሰላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ማንያዘዋል ለማ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ጽህፈት ቤቱ በኢተያ ጎንዴ በራሱ እርሻ፣ በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች እና በባለሀብቶች እርሻ ላይ ዘር እያባዛ መሆኑን ተናግረዋል።

እነዚህን የዘር ዓይነቶችም አሰላ በሚገኘው የዘር ማበጠሪያ ማሽን በማዘጋጀት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ለተያዘው የበጋ መስኖም 11ሺህ 519 ኩንታል የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የስንዴ ምርጥ ዘር ለሁሉም ክልሎች ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
እስካሁንም ከ5ሺህ ኩንታል በላይ ማሰራጨቱን ጠቁመው፤ ቀሪዎቹንም በፍጥነት በማሰራጨት ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
በማሰራጨት ላይ የሚገኙ ዝርያዎች ምርታማነታቸው ከፍተኛ የሆኑና በሽታን መቋቋም የሚችሉ የሰብል ዓይነቶች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።

ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ከሚያስችሉ ግብዓቶች መካከል ምርጥ ዘር በስፋት ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025