🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሕዳር 16/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የአሰላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለበጋ መስኖ እርሻ የሚውል ከአስራ አንድ ሺህ አምስት መቶ ኩንታል በላይ የስንዴ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እያሰራጨ መሆኑን ገለጸ።
ጽህፈት ቤቱ የአርሶ አደሩን የምርጥ ዘር ፍላጎት ለማሟላት በራሱ፣ በክላስተር የተደራጁ አርሶ አደሮች እና ሰፋፊ እርሻ ባላቸው ባለሃብቶች መሬት ላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን ምርጥ ዘሮች በማባዛት ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በዚህም ስንዴን ጨምሮ በበርካታ የሰብል ዓይነቶች እና ዝርያዎች መስራች፣ ቅድመ መስራች እና የተመሰከረለት የዘር ደረጃዎችን በማባዛት ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የአሰላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ማንያዘዋል ለማ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ጽህፈት ቤቱ በኢተያ ጎንዴ በራሱ እርሻ፣ በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች እና በባለሀብቶች እርሻ ላይ ዘር እያባዛ መሆኑን ተናግረዋል።

እነዚህን የዘር ዓይነቶችም አሰላ በሚገኘው የዘር ማበጠሪያ ማሽን በማዘጋጀት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ለተያዘው የበጋ መስኖም 11ሺህ 519 ኩንታል የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የስንዴ ምርጥ ዘር ለሁሉም ክልሎች ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
እስካሁንም ከ5ሺህ ኩንታል በላይ ማሰራጨቱን ጠቁመው፤ ቀሪዎቹንም በፍጥነት በማሰራጨት ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
በማሰራጨት ላይ የሚገኙ ዝርያዎች ምርታማነታቸው ከፍተኛ የሆኑና በሽታን መቋቋም የሚችሉ የሰብል ዓይነቶች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።

ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ከሚያስችሉ ግብዓቶች መካከል ምርጥ ዘር በስፋት ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025