የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ የስንዴ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እያሰራጨ ነው

Nov 26, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሕዳር 16/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የአሰላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለበጋ መስኖ እርሻ የሚውል ከአስራ አንድ ሺህ አምስት መቶ ኩንታል በላይ የስንዴ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሩ እያሰራጨ መሆኑን ገለጸ።

ጽህፈት ቤቱ የአርሶ አደሩን የምርጥ ዘር ፍላጎት ለማሟላት በራሱ፣ በክላስተር የተደራጁ አርሶ አደሮች እና ሰፋፊ እርሻ ባላቸው ባለሃብቶች መሬት ላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን ምርጥ ዘሮች በማባዛት ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።

በዚህም ስንዴን ጨምሮ በበርካታ የሰብል ዓይነቶች እና ዝርያዎች መስራች፣ ቅድመ መስራች እና የተመሰከረለት የዘር ደረጃዎችን በማባዛት ላይ እንደሚገኝም ተገልጿል።

በኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን የአሰላ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ተወካይ አቶ ማንያዘዋል ለማ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ጽህፈት ቤቱ በኢተያ ጎንዴ በራሱ እርሻ፣ በክላስተር በተደራጁ አርሶ አደሮች እና በባለሀብቶች እርሻ ላይ ዘር እያባዛ መሆኑን ተናግረዋል።


እነዚህን የዘር ዓይነቶችም አሰላ በሚገኘው የዘር ማበጠሪያ ማሽን በማዘጋጀት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ለተያዘው የበጋ መስኖም 11ሺህ 519 ኩንታል የተለያዩ ዝርያ ያላቸውን የስንዴ ምርጥ ዘር ለሁሉም ክልሎች ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

እስካሁንም ከ5ሺህ ኩንታል በላይ ማሰራጨቱን ጠቁመው፤ ቀሪዎቹንም በፍጥነት በማሰራጨት ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

በማሰራጨት ላይ የሚገኙ ዝርያዎች ምርታማነታቸው ከፍተኛ የሆኑና በሽታን መቋቋም የሚችሉ የሰብል ዓይነቶች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።


ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ከሚያስችሉ ግብዓቶች መካከል ምርጥ ዘር በስፋት ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026