የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ በምግብ ራስን በመቻል ከተረጂነት ለመወጣት እየተከናወኑ ባሉ ሥራዎች ውጤት እየተመዘገበ ነው

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ሆሳዕና፤ ሕዳር 18/2018(ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምግብ ራስን በመቻል ከተረጂነት ለመወጣት እየተከናወኑ ባሉ ሥራዎች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገለፀ፡፡

ኮሚሽኑ በማረቆ ልዩ ወረዳ ቢዳራ ቀበሌ በ30 ሄክታር መሬት ላይ ያለማው የደረሰ የበቆሎ ሰብልን የማሰባሰብ ሥራ ዛሬ አስጀምሯል፡፡

የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ማዕረጉ ማቲዎስ በዚህ ወቅት እንደገለጹት በክልሉ በምግብ ራስን በመቻል ከተረጂነት ለመወጣት እየተከናወኑ ባሉ ሥራዎች ተስፋ ሰጪ ውጤት እየተመዘገበ ነው፡፡

ተረጂነት ዜጎች ያላቸውን አማራጮች ተጠቅመው እንዳይሰሩ ያደርጋል ያሉት ኮሚሽነሩ በክልሉ በተረጂነት ውስጥ ከሚገኙ ዜጎች ጋር ከችግሩ እንዲወጡ የጋራ ተግባቦት መፈጠሩን ገልጸዋል።

በክልሉ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን በመቻል ከተረጂነት ለመውጣት በተሰራው ሥራ ተጨባጭ ውጤት እየተገኘ መምጣቱንም ተናግረዋል፡፡


በዚህም በክልሉ በተረጂነት ውስጥ የነበሩ ከ318ሺህ 644 በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን የማሸጋገር ሥራ ተሰርቷል ብለዋል፡፡

ከተረጂነት የተሸጋገሩ የማህበረሰብ ክፍሎች በቤተሰብ ጥሪት የምግብ ዋስትናን እንዲያረጋግጡ ከማድረግ በተጨማሪ የድጋፍና ክትትል ሥራ በማከናወን ራሳቸውን እንዲያበቁ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በክልሉ የሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለማከናወን የተጀመረውን ጥረት ስኬታማ ለማድረግ በበጀት ዓመቱ 1ሺህ 431 ሄክታር ማሳ በስንዴና በበቆሎ ሰብሎች መልማቱን ገልጸዋል፡፡

የሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን መንግሥት እያከናወነ ካለው ተግባር በተጨማሪ የማህበረሰቡን የእርስ በርስ መደጋገፍ እሴት በማጠናከር በዘርፉ የታለመውን ውጤት ለማምጣት በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል።


በኮሚሽኑ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ዝግጁነት ፕሮጀክት ፅህፈት ቤት ኃላፊ ሙርሰል አማን በበኩላቸው በክልሉ ለሚከሰቱ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ክስተቶች በሰብዓዊ ድጋፍ በራስ አቅም ምላሽ መስጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።


ለዚህም በ2017 እና በተያዘው በጀት ዓመት 100 ሺህ ኩንታል የመጠባበቂያ እህል ለማከማቸትና 120 ሚሊዮን ብር የመጠባበቂያ ፈንድ ለመያዝ ግብ ተይዞ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በማረቆ ልዩ ወረዳ ዛሬ የተጀመረው የበቆሎ ምርት ማሰባሰብ ሥራ የዚሁ አካል መሆኑንም ገልፀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025