🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤ ሕዳር 18/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያን ቁልፍ የትኩረት መስኮች ባማከለ መልኩ አጋርነታቸውን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ።
የአፍሪካ የፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ፎረም በሞሮኮ ራባት ተካሄዷል።
የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከፎረሙ ጎን ለጎን ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ ጋር ተወያይተዋል።
ውይይቱ የበጀት ድጋፍን ማጠናከር፣ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያን ጨምሮ በሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የተቀናጀ የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲኖር ማድረግ እና ኢትዮጵያ የምታዘጋጀውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ በፋይናንስ መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ያላቸው የቆየ አጋርነትም በውይይቱ ላይ ተነስቷል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ ባንኩ ለኢትዮጵያ የልማት ስራዎች እየተወጣ ያለውን ወሳኝ ሚናም አንስተዋል።
ባንኩ የኢትዮጵያን ግዙፍ ፕሮጀክቶች በፋይናንስ ለመደገፍ ያለውን ዝግጁነት አድንቀዋል።
የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የሪፎርም ሂደት ያደነቁ ሲሆን ባንኩ በኢትዮጵያ የግል ኢንቨስትመንትን በሚያሳድጉ እና የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት በሚፈጥሩ መስኮች ላይ የሚያደርገውን ድጋፍ ለማጠናከር ፍላጎት እንዳለው አመልክተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ እና የባንኩ ፕሬዝዳንት በውይይቱ ላይ ተከታታይና የቴክኒክ ምክክሮችን ለማጠናከር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋርነታቸውን በዘላቂ ልማት፣ ቀጣናዊ ትስስር እና የግሉ ዘርፍ እድገት በሚያጠናክር መልኩ ለማጎልበት እንደሚሰሩ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026