የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋርነታቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ

Nov 28, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ሕዳር 18/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያን ቁልፍ የትኩረት መስኮች ባማከለ መልኩ አጋርነታቸውን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን አስታወቁ።

የአፍሪካ የፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ፎረም በሞሮኮ ራባት ተካሄዷል።

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ ከፎረሙ ጎን ለጎን ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ የበጀት ድጋፍን ማጠናከር፣ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያን ጨምሮ በሌሎች ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች የተቀናጀ የኢንቨስትመንት ፍሰት እንዲኖር ማድረግ እና ኢትዮጵያ የምታዘጋጀውን 32ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ በፋይናንስ መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረ ነው።

ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ያላቸው የቆየ አጋርነትም በውይይቱ ላይ ተነስቷል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ ባንኩ ለኢትዮጵያ የልማት ስራዎች እየተወጣ ያለውን ወሳኝ ሚናም አንስተዋል።

ባንኩ የኢትዮጵያን ግዙፍ ፕሮጀክቶች በፋይናንስ ለመደገፍ ያለውን ዝግጁነት አድንቀዋል።

የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ (ዶ/ር) የኢትዮጵያን የሪፎርም ሂደት ያደነቁ ሲሆን ባንኩ በኢትዮጵያ የግል ኢንቨስትመንትን በሚያሳድጉ እና የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት በሚፈጥሩ መስኮች ላይ የሚያደርገውን ድጋፍ ለማጠናከር ፍላጎት እንዳለው አመልክተዋል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ እና የባንኩ ፕሬዝዳንት በውይይቱ ላይ ተከታታይና የቴክኒክ ምክክሮችን ለማጠናከር ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አጋርነታቸውን በዘላቂ ልማት፣ ቀጣናዊ ትስስር እና የግሉ ዘርፍ እድገት በሚያጠናክር መልኩ ለማጎልበት እንደሚሰሩ መግለጻቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢዜአ በላከው መረጃ አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025