🔇Unmute
ባሕርዳር ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የቅዳሜና እሀድን ጨምሮ የተለያዩ የገበያ አማራጮች በመስፋፋታቸው ገበያን በማረጋጋት ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ኢብራሂም መሀመድ (ዶ/ር) ዛሬ በሰጡት መግለጫ ላይ እንዳመለከቱት፤ ሕገወጥ ንግድን በመከላከል ገበያ የማረጋጋቱ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል።
በዚህም በስምንት ከተሞች የተገነቡ ዘመናዊ የገበያ ማዕከላትን ወደ ስራ በማስገባት፣ የቅዳሜና እሁድ ገበያን በማስፋት ከ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለሸማቹ ሕብረተሰብ በቀጥታ እየቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
እየቀረበ ያለውም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ከአንድ ቢሊዮን 270 ሚሊዮን ብር በላይ ተዘዋዋሪ ብድር ለሸማች ሕብረት ስራ ማሕበራትና ለዩኒየኖች በማመቻቸት እንደሆነ አስረድተዋል።
በየከተሞቹ የተገነቡት የገበያ ማዕከላትም አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ ዋጋን በማረጋጋት ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል።
በተከናወነው ስራም የግብርና ምርት ዋጋ በየጊዜው እየቀነሰና ገበያው እየተረጋጋ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ይህም የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም ስምንት ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ለተጠቃሚው ሕብረተሰብ ማቅረብ መቻሉንም አንስተዋል።
ገበያን ለማረጋጋት እየተደረገ ካለው ተግባር ጎን ለጎንም መንግስት ለሠራተኛው ያደረገውን የደመወዝ ጭማሪ ተከትሎ ምርትን በሕገወጥ መንገድ በደበቁ 308 ድርጅቶችና የዋጋ ዝርዝር ሳይለጥፉ በተገኙ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱንም ጠቅሰዋል።
በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 117 ሺህ ሊትር ነዳጅ መያዙንም አረጋግጠዋል።
ለዋጋ ጭማሬ ምክንያት የነበሩና በተለያዩ ከተሞች ተቋቁመው ቀረጥ ያስከፍሉ የነበሩ ኬላዎች እንዲነሱ መደረጉን ጠቅሰው፤ ተግባሩን ለመከላከል ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ሕገወጥ ንግድን በተቀናጀና በተናበበ አግባብ በመከላከልና በመቆጣጠር ጤናማ የግብይት ስርዓት እንዲፈጠር የክትትልና ቁጥጥር ተግባሩ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የቢሮው ኃላፊ ኢብራሂም መሀመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026