🔇Unmute
ባሕርዳር ፤ ሕዳር 23/2018 (ኢዜአ) ፡- በአማራ ክልል የቅዳሜና እሀድን ጨምሮ የተለያዩ የገበያ አማራጮች በመስፋፋታቸው ገበያን በማረጋጋት ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ ኢብራሂም መሀመድ (ዶ/ር) ዛሬ በሰጡት መግለጫ ላይ እንዳመለከቱት፤ ሕገወጥ ንግድን በመከላከል ገበያ የማረጋጋቱ ተግባር በትኩረት እየተከናወነ ይገኛል።
በዚህም በስምንት ከተሞች የተገነቡ ዘመናዊ የገበያ ማዕከላትን ወደ ስራ በማስገባት፣ የቅዳሜና እሁድ ገበያን በማስፋት ከ3 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለሸማቹ ሕብረተሰብ በቀጥታ እየቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
እየቀረበ ያለውም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ከአንድ ቢሊዮን 270 ሚሊዮን ብር በላይ ተዘዋዋሪ ብድር ለሸማች ሕብረት ስራ ማሕበራትና ለዩኒየኖች በማመቻቸት እንደሆነ አስረድተዋል።
በየከተሞቹ የተገነቡት የገበያ ማዕከላትም አምራችና ሸማቹን በቀጥታ በማገናኘት የገበያ ዋጋን በማረጋጋት ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል።
በተከናወነው ስራም የግብርና ምርት ዋጋ በየጊዜው እየቀነሰና ገበያው እየተረጋጋ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ይህም የበለጠ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም ስምንት ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ለተጠቃሚው ሕብረተሰብ ማቅረብ መቻሉንም አንስተዋል።
ገበያን ለማረጋጋት እየተደረገ ካለው ተግባር ጎን ለጎንም መንግስት ለሠራተኛው ያደረገውን የደመወዝ ጭማሪ ተከትሎ ምርትን በሕገወጥ መንገድ በደበቁ 308 ድርጅቶችና የዋጋ ዝርዝር ሳይለጥፉ በተገኙ ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱንም ጠቅሰዋል።
በሕገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተገኘ 117 ሺህ ሊትር ነዳጅ መያዙንም አረጋግጠዋል።
ለዋጋ ጭማሬ ምክንያት የነበሩና በተለያዩ ከተሞች ተቋቁመው ቀረጥ ያስከፍሉ የነበሩ ኬላዎች እንዲነሱ መደረጉን ጠቅሰው፤ ተግባሩን ለመከላከል ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ሕገወጥ ንግድን በተቀናጀና በተናበበ አግባብ በመከላከልና በመቆጣጠር ጤናማ የግብይት ስርዓት እንዲፈጠር የክትትልና ቁጥጥር ተግባሩ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የቢሮው ኃላፊ ኢብራሂም መሀመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025