🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 26/2018 (ኢዜአ)፡- የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርዓት ነዋሪዎች ዘመናዊ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችላቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቱዩት የለማውን የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርዓትን ዛሬ አስጀምረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዲጂታል ስርዓቱ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ተገልጋዮች ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያግዝ ነው።
ከዚህ በፊት የነበረውን የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎችን አገልግሎት አሰጣጥ ሙሉ በሙሉ የሚቀይር መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዲጂታል ስርዓቱ የአዲስ አበባን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ መሆኑን በማንሳት፤ ከሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ50 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ ይጀምራል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቱዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፤ እንደ ሀገር ፈጣን ዕድገት ለማስመዝገብ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው፤ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ እመርታዊ ለውጥ እያስመዘገበች ነው ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025