የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርዓት ነዋሪዎች ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል

Dec 8, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ህዳር 26/2018 (ኢዜአ)፡- የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርዓት ነዋሪዎች ዘመናዊ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችላቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቱዩት የለማውን የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርዓትን ዛሬ አስጀምረዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዲጂታል ስርዓቱ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ተገልጋዮች ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያግዝ ነው።

ከዚህ በፊት የነበረውን የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎችን አገልግሎት አሰጣጥ ሙሉ በሙሉ የሚቀይር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዲጂታል ስርዓቱ የአዲስ አበባን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ መሆኑን በማንሳት፤ ከሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ50 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ ይጀምራል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቱዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፤ እንደ ሀገር ፈጣን ዕድገት ለማስመዝገብ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው፤ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ እመርታዊ ለውጥ እያስመዘገበች ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025