🔇Unmute
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 26/2018 (ኢዜአ)፡- የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርዓት ነዋሪዎች ዘመናዊ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት የሚያስችላቸው መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቱዩት የለማውን የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርዓትን ዛሬ አስጀምረዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ዲጂታል ስርዓቱ አገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ተገልጋዮች ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያግዝ ነው።
ከዚህ በፊት የነበረውን የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎችን አገልግሎት አሰጣጥ ሙሉ በሙሉ የሚቀይር መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዲጂታል ስርዓቱ የአዲስ አበባን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት የሚያሳድግ መሆኑን በማንሳት፤ ከሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ50 ወረዳዎች ተግባራዊ መደረግ ይጀምራል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቱዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፤ እንደ ሀገር ፈጣን ዕድገት ለማስመዝገብ ቴክኖሎጂዎችን ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበች መሆኑን ገልጸው፤ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፍ እመርታዊ ለውጥ እያስመዘገበች ነው ብለዋል፡፡
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025