የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የዲላ ከተማ የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የሥራ ዕድል እየፈጠረ ነው

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

ዲላ ፤ታህሳስ 2/2018 (ኢዜአ)፡-በዲላ ከተማ እየተገነባ ያለው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ።

የከተማ አስተዳደሩ በበኩሉ በከተማው በሁለተኛ ምዕራፍ እየተከናወነ ያለው የ10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ሥራ እየተፋጠነ መሆኑን አስታውቋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የዲላ ከተማ ነዋሪዎች እንዳሉት የኮሪደር ልማቱ ለከተማዋ ካጎናጸፋት ውበት ባለፈ ዜጎች በተለያዩ የሥራ ዘርፎች እንዲሰማሩ የሥራ እድል እየፈጠረ ነው።

በከተማው በአትክልት ንግድ ሥራ የተሰማሩት ወይዘሮ ትግስት ታምራት እንዳሉት የኮሪደር ልማቱ ጽዱ አካባቢዎች መፍጠር እንደቻለ ተናግረዋል።

ይህም የከተማዋን የጽዳትና የውበት ደረጃ ከማሻሻል ባለፈ እሳቸውም የንግድ ሥራቸውን ንጹህና ጽዱ በሆነ አካባቢ ለማከናወን እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራው ቀደም ሲል ለእይታ የማይስቡና ቆሻሻ መጣያ ጭምር የነበሩ ስፍራዎችን ወደ መዝናኛነት የቀየረ መሆኑን ያነሱት ደግሞ ሌላዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ መሰረት አበበ ናቸው።

ልማቱ የከተማዋን ገጽታ እንዲቀየር ከማድረግ ባለፈ ለዜጎች የሥራ እድል እየፈጠረ መምጣቱን ገልጸው፣ በርካታ ሰዎች በኮሪደር በለሙ አካባቢዎች የንግድ ሥራ ጀምረው ገቢ እያገኙ መሆኑን ገልጸዋል።

ለልማቱ መሳካት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ የተናገሩት አስተያየት ሰጪዋ የተለወጡ አካባቢዎችን የመጠበቅና አረንጓዴ ስፍራዎችን የመንከባከብ ሥራ እንደሚያከናወኑም ተናግረዋል።

የዲላ ከተማ ከንቲባ መስፍን ደምሴ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት በከተማው በመጀመሪያ ምዕራፍ የተከናወነው የ11 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት የከተማዋን ደረጃ በማሻሻል ለኑሮና ኢንቨስትመንት ተመራጭ አድርጓታል።

በሁለተኛው ምዕራፍም ከተሽከርካሪና እግረኛ መንገድ በተጨማሪ የወንዝ ዳርቻ ልማት፣ የአረንጋዴ ልማት እንዲሁም መዝናኛ ቦታዎችን ያካተተ 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ስራ እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል።

ልማቱ በህብረተሰብ ተሳትፎ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት ከንቲባው፣ በተለይ የከተማው ነዋሪ ይዞታውን በመልቀቅና ግብዓት በማቅረብ እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲጠቅል አስገንዝበዋል።

የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታና ውበት ከመቀየር ባለፈ ለዜጎችም የሥራ እድል እየፈጠረ በመሆኑ ህብረተሰቡ በኮሪደር ለለሙ አካባቢዎች አስፈላጊውን ጥበቃና እንክብካቤ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025