የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የኢንስቲትዩቱ ስራ መጀመር ዘመናዊ የፋይናንስ ስርዓት ለመገንባትና ለኢኮኖሚ ዕድገት ሚናው የጎላ ነው

Dec 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ስራ መጀመር ዘመናዊና አስተማማኝ የፋይናንስ ስርዓት በመገንባት ለአጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።

የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝ እና ኦዲት ቦርድ ለተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ስያሜ ይፋ የማድረግና የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የኢንስቲትዩቱ ወደ ስራ መግባት የፋይናንስ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽንን ለማሳለጥ ወሳኝ ነው።

በተጨማሪም ለፋይናንስ ስርዓቱ የጀርባ አጥንት ከመሆን ባለፈ አስተማማኝ የፋይናንስ ዘርፍ እንዲፈጠር፣ ህብረተሰቡ ስለፋይናንስ ዘርፉ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው እና ለውሳኔ ሰጪዎች ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ነው ያሉት።

ይህም የኢኮኖሚ ዕድገትና ሽግግርን በማሳለጥ ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ጠቅሰዋል።

ካሁን ቀደም የሂሳብ ባለሙያዎች ማረጋገጫ የሚቀበሉት ከውጭ ተቋማት መሆኑን በማውሳት፥ በይፋ ስራ የጀመረው የተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ይህንኑ ተግባር በሀገር ውስጥ ማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል።

ኢንስቲትዩቱ በተቋማት አሠራር ግልፅነትና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ የሂሳብ አያያዝ፣ ኦዲት እና የፋይናንሺያል ሪፖርት መረጃዎችን የማስተዋወቅ እና የማሳደግ አላማ እንዳለውም ጠቅሰዋል።


ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በየዓመቱ በርካታ የሂሳብ ባለሙያዎች የሚመረቁ ቢሆንም በኢትዮጵያ ያሉት የተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ቁጥር ግን በጣም አነስተኛ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።

የባለሙያዎችን ብቃት በማረጋገጥ ይህንኑ ችግር እንደሚፈታ የታመነበት ኢንስቲትዩት ዛሬ ሥራውን በይፋ መጀመሩ ተገልጿል።

በመድረኩ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ፣ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የዓለም ባንክ ተወካዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025