🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 2/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ስራ መጀመር ዘመናዊና አስተማማኝ የፋይናንስ ስርዓት በመገንባት ለአጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ።
የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝ እና ኦዲት ቦርድ ለተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ስያሜ ይፋ የማድረግና የስራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር እያካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ የተገኙት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የኢንስቲትዩቱ ወደ ስራ መግባት የፋይናንስ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽንን ለማሳለጥ ወሳኝ ነው።
በተጨማሪም ለፋይናንስ ስርዓቱ የጀርባ አጥንት ከመሆን ባለፈ አስተማማኝ የፋይናንስ ዘርፍ እንዲፈጠር፣ ህብረተሰቡ ስለፋይናንስ ዘርፉ በቂ ግንዛቤ እንዲኖረው እና ለውሳኔ ሰጪዎች ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ነው ያሉት።
ይህም የኢኮኖሚ ዕድገትና ሽግግርን በማሳለጥ ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ጠቅሰዋል።
ካሁን ቀደም የሂሳብ ባለሙያዎች ማረጋገጫ የሚቀበሉት ከውጭ ተቋማት መሆኑን በማውሳት፥ በይፋ ስራ የጀመረው የተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ኢንስቲትዩት ይህንኑ ተግባር በሀገር ውስጥ ማከናወን የሚያስችል ነው ብለዋል።
ኢንስቲትዩቱ በተቋማት አሠራር ግልፅነትና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ የሂሳብ አያያዝ፣ ኦዲት እና የፋይናንሺያል ሪፖርት መረጃዎችን የማስተዋወቅ እና የማሳደግ አላማ እንዳለውም ጠቅሰዋል።

ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በየዓመቱ በርካታ የሂሳብ ባለሙያዎች የሚመረቁ ቢሆንም በኢትዮጵያ ያሉት የተመሰከረላቸው የሂሳብ ባለሙያዎች ቁጥር ግን በጣም አነስተኛ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።
የባለሙያዎችን ብቃት በማረጋገጥ ይህንኑ ችግር እንደሚፈታ የታመነበት ኢንስቲትዩት ዛሬ ሥራውን በይፋ መጀመሩ ተገልጿል።
በመድረኩ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ፣ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ(ዶ/ር) እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የዓለም ባንክ ተወካዮች ተገኝተዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026