የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በገናና የጥምቀት በዓላት ለመታደም የሚመጡ ጎብኝዎች አዳዲስ የመስህብ ሥፍራዎችን የሚጎበኙበት ዕድል ተመቻችቷል

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦በገናና የጥምቀት በዓላት ለመታደም የሚመጡ ጎብኝዎች አዳዲስ የመስህብ ሥፍራዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ።

በኢትዮጵያ በድምቀት ከሚከበሩ ኃይማኖታዊና የአደባባይ በዓላት መካከል ገናና ጥምቀት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

በዓላቱ የኢትዮጵያን ታሪካዊና ኃይማኖታዊ እሴት ለውጭ ጎብኚዎች በአግባቡ ለማስተዋወቅ ጉልህ ሚና ይጫወታሉ።

በተለይም ገና እና ጥምቀት ላሊበላና ጎንደርን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ የሚከበር ሲሆን በዓሉን ለመታደም የሚመጡ የውጭ ቱሪስቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መጥቷል፡፡


በአዲስ አበባ የተገነቡ በርካታ የቱሪስት መዳረሻዎች አሁን ላይ ከውጭ ሀገር ባለፈ የሀገር ውስጥ የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንዲያድግ ከፍተኛ ሚና በመጫወት ላይ ናቸው፡፡

የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የገናና የጥምቀት በዓላት ከእምነቱ ተከታዮች ባሻገር የውጭ ጎብኝዎችን ቀልብ የሚስቡ ታላላቅ ዓመታዊ ክብረ በዓላት ናቸው።

በበዓላቱ ለመታደም የሚመጡ ጎብኚዎች የኢትዮጵያን የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ቅርሶችንና የአደባባይ በዓላትን በማስተዋወቅ ለቱሪዝም ዕድገት ወሳኝ ዕድሎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዚህም በበዓላቱ ለመታደም የሚመጡ ጎብኝዎች የተሻለ የቆይታ እንዲኖራቸው ማድረግ የሚያስችል አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።


የገናና የጥምቀት በዓላት በድምቀት በሚከበርባቸው አካባቢዎችም ለባለድርሻ አካላት ሥልጠና በመስጠት የቱሪስቶችን የአገልግሎት እርካታ ለማሳደግ ዝግጅት መደረጉን አንስተዋል።

ከዓለም ክፍሎች በገናና የጥምቀት በዓላት ለመታደም ለሚመጡ ጎብኝዎችም በተለያዩ የመረጃ አማራጮች የበዓላቱን ታሪካዊ ዳራና በድምቀት የሚከበርባቸወን ሥፍራዎች የማስተዋወቅ ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቱሪዝም ሚኒስቴር አስተባባሪነት አስጎብኝዎችና ባለድርሻ አካላት አዳዲስ የመስህብ ስፍራዎችን በማስተዋወቅ ጭምር የጎብኝዎችን የቆይታ ጊዜ የተሻለ የሚያድርግ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።


በተቀረጹ የጉብኝት ፓኬጆችም የገናና የጥምቀት በዓላትን ለመታደም የሚመጡ ጎብኝዎች አዳዲስ የመስህብ ሥፍራዎችን የሚጎበኙበት ዕድል መመቻቸቱን አስታውቀዋል።

የጎብኝዎችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም የተሻለ የጉብኝት ምኅዳር ለመፍጠርም አስጎብኝዎች፣ ሆቴሎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025