የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአዳማ ከተማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ምርቶች እና ሸቀጦች በስፋት ቀርበዋል

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የእርድ እንስሳትን ጨምሮ ምርቶች እና ሸቀጦች በስፋት መቅረባቸውን ነጋዴዎች እና ሸማቾች ገለፁ።

ኢዜአ ካነጋገራቸው ሸማቾች መካከል አቶ ነጋሽ ሃይሌ በሰጡት አስተያየት፤ ለገና በዓል ከጎረቤቶቻቸው ጋር ለቅርጫ የሚሆን በሬ ለመግዛት መምጣታቸውን ገልጸው ለበዓሉ የሰንጋና የድልብ በሬዎች በቂ አቅርቦት እንዳለ ተናግረዋል።


አቅርቦቱ በበቂ መጠን ቢኖርም የበሬ ዋጋ ከአምና ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ማሳየቱን ገልጸዋል።

ወይዘሮ ለምለም ቃሲም በበኩላቸው፤ የእርድ እንስሳት ገበያው ካለፈው የገና በዓል ጋር ሲነፃፀር በአቅርቦት በኩል የአሁኑ የተሻለ ነው ብለዋል።

የሀበሻ ዶሮ በአንድ ሺህ 500 ብር መግዛታቸውን ጠቅሰው በከተማዋ ለበዓል የሚያስፈልጉ ሸቀጣ ሸቀጦችን ጨምሮ የእርድ እንስሳት አቅርቦት ችግር እንደሌለ መታዘባቸውን ተናግረዋል።

ሰንጋ በሬዎችን ለገበያ ያቀረቡት ሳሀሊ ሀጂ ከድር፣ ከ80 ሺህ እስከ 100 ሺህ ብር በሆነ ዋጋ እየሸጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በከተማው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለገና በዓል በዛር እና ኤግዚቢሽን ያዘጋጀው የአዳማ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሥራ አስኪያጅ አቶ ብዙነህ ግርማ፣ በባዛሩ ላይ የተለያዩ ምርቶችና ሸቀጦች በስፋት መቅረባቸውን ገልጸዋል።

በባዛሩ ላይ የጎጆ ኢንዱስትሪዎች፣ ፋብሪካዎች፣ አምራች ኢንተርፕራይዞች፣ ነጋዴዎች፣ የሕብረት ስራ ማህበራትና የተለያዩ አንቀሳቃሾች መሳተፋቸውን ተናግረዋል።


በዚህም ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በስፋት መቅረባቸውን አመላክተዋል።

ሕብረተሰቡም ከእንቁላል ጀምሮ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የተለያዩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመቱ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026