የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአዳማ ከተማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ምርቶች እና ሸቀጦች በስፋት ቀርበዋል

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የእርድ እንስሳትን ጨምሮ ምርቶች እና ሸቀጦች በስፋት መቅረባቸውን ነጋዴዎች እና ሸማቾች ገለፁ።

ኢዜአ ካነጋገራቸው ሸማቾች መካከል አቶ ነጋሽ ሃይሌ በሰጡት አስተያየት፤ ለገና በዓል ከጎረቤቶቻቸው ጋር ለቅርጫ የሚሆን በሬ ለመግዛት መምጣታቸውን ገልጸው ለበዓሉ የሰንጋና የድልብ በሬዎች በቂ አቅርቦት እንዳለ ተናግረዋል።


አቅርቦቱ በበቂ መጠን ቢኖርም የበሬ ዋጋ ከአምና ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ማሳየቱን ገልጸዋል።

ወይዘሮ ለምለም ቃሲም በበኩላቸው፤ የእርድ እንስሳት ገበያው ካለፈው የገና በዓል ጋር ሲነፃፀር በአቅርቦት በኩል የአሁኑ የተሻለ ነው ብለዋል።

የሀበሻ ዶሮ በአንድ ሺህ 500 ብር መግዛታቸውን ጠቅሰው በከተማዋ ለበዓል የሚያስፈልጉ ሸቀጣ ሸቀጦችን ጨምሮ የእርድ እንስሳት አቅርቦት ችግር እንደሌለ መታዘባቸውን ተናግረዋል።

ሰንጋ በሬዎችን ለገበያ ያቀረቡት ሳሀሊ ሀጂ ከድር፣ ከ80 ሺህ እስከ 100 ሺህ ብር በሆነ ዋጋ እየሸጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በከተማው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለገና በዓል በዛር እና ኤግዚቢሽን ያዘጋጀው የአዳማ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሥራ አስኪያጅ አቶ ብዙነህ ግርማ፣ በባዛሩ ላይ የተለያዩ ምርቶችና ሸቀጦች በስፋት መቅረባቸውን ገልጸዋል።

በባዛሩ ላይ የጎጆ ኢንዱስትሪዎች፣ ፋብሪካዎች፣ አምራች ኢንተርፕራይዞች፣ ነጋዴዎች፣ የሕብረት ስራ ማህበራትና የተለያዩ አንቀሳቃሾች መሳተፋቸውን ተናግረዋል።


በዚህም ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በስፋት መቅረባቸውን አመላክተዋል።

ሕብረተሰቡም ከእንቁላል ጀምሮ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የተለያዩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመቱ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025