🔇Unmute
አዳማ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የእርድ እንስሳትን ጨምሮ ምርቶች እና ሸቀጦች በስፋት መቅረባቸውን ነጋዴዎች እና ሸማቾች ገለፁ።
ኢዜአ ካነጋገራቸው ሸማቾች መካከል አቶ ነጋሽ ሃይሌ በሰጡት አስተያየት፤ ለገና በዓል ከጎረቤቶቻቸው ጋር ለቅርጫ የሚሆን በሬ ለመግዛት መምጣታቸውን ገልጸው ለበዓሉ የሰንጋና የድልብ በሬዎች በቂ አቅርቦት እንዳለ ተናግረዋል።

አቅርቦቱ በበቂ መጠን ቢኖርም የበሬ ዋጋ ከአምና ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ማሳየቱን ገልጸዋል።
ወይዘሮ ለምለም ቃሲም በበኩላቸው፤ የእርድ እንስሳት ገበያው ካለፈው የገና በዓል ጋር ሲነፃፀር በአቅርቦት በኩል የአሁኑ የተሻለ ነው ብለዋል።
የሀበሻ ዶሮ በአንድ ሺህ 500 ብር መግዛታቸውን ጠቅሰው በከተማዋ ለበዓል የሚያስፈልጉ ሸቀጣ ሸቀጦችን ጨምሮ የእርድ እንስሳት አቅርቦት ችግር እንደሌለ መታዘባቸውን ተናግረዋል።
ሰንጋ በሬዎችን ለገበያ ያቀረቡት ሳሀሊ ሀጂ ከድር፣ ከ80 ሺህ እስከ 100 ሺህ ብር በሆነ ዋጋ እየሸጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በከተማው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለገና በዓል በዛር እና ኤግዚቢሽን ያዘጋጀው የአዳማ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሥራ አስኪያጅ አቶ ብዙነህ ግርማ፣ በባዛሩ ላይ የተለያዩ ምርቶችና ሸቀጦች በስፋት መቅረባቸውን ገልጸዋል።
በባዛሩ ላይ የጎጆ ኢንዱስትሪዎች፣ ፋብሪካዎች፣ አምራች ኢንተርፕራይዞች፣ ነጋዴዎች፣ የሕብረት ስራ ማህበራትና የተለያዩ አንቀሳቃሾች መሳተፋቸውን ተናግረዋል።

በዚህም ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በስፋት መቅረባቸውን አመላክተዋል።
ሕብረተሰቡም ከእንቁላል ጀምሮ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የተለያዩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመቱ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026