የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በአዳማ ከተማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ምርቶች እና ሸቀጦች በስፋት ቀርበዋል

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የእርድ እንስሳትን ጨምሮ ምርቶች እና ሸቀጦች በስፋት መቅረባቸውን ነጋዴዎች እና ሸማቾች ገለፁ።

ኢዜአ ካነጋገራቸው ሸማቾች መካከል አቶ ነጋሽ ሃይሌ በሰጡት አስተያየት፤ ለገና በዓል ከጎረቤቶቻቸው ጋር ለቅርጫ የሚሆን በሬ ለመግዛት መምጣታቸውን ገልጸው ለበዓሉ የሰንጋና የድልብ በሬዎች በቂ አቅርቦት እንዳለ ተናግረዋል።


አቅርቦቱ በበቂ መጠን ቢኖርም የበሬ ዋጋ ከአምና ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ማሳየቱን ገልጸዋል።

ወይዘሮ ለምለም ቃሲም በበኩላቸው፤ የእርድ እንስሳት ገበያው ካለፈው የገና በዓል ጋር ሲነፃፀር በአቅርቦት በኩል የአሁኑ የተሻለ ነው ብለዋል።

የሀበሻ ዶሮ በአንድ ሺህ 500 ብር መግዛታቸውን ጠቅሰው በከተማዋ ለበዓል የሚያስፈልጉ ሸቀጣ ሸቀጦችን ጨምሮ የእርድ እንስሳት አቅርቦት ችግር እንደሌለ መታዘባቸውን ተናግረዋል።

ሰንጋ በሬዎችን ለገበያ ያቀረቡት ሳሀሊ ሀጂ ከድር፣ ከ80 ሺህ እስከ 100 ሺህ ብር በሆነ ዋጋ እየሸጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በከተማው ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለገና በዓል በዛር እና ኤግዚቢሽን ያዘጋጀው የአዳማ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሥራ አስኪያጅ አቶ ብዙነህ ግርማ፣ በባዛሩ ላይ የተለያዩ ምርቶችና ሸቀጦች በስፋት መቅረባቸውን ገልጸዋል።

በባዛሩ ላይ የጎጆ ኢንዱስትሪዎች፣ ፋብሪካዎች፣ አምራች ኢንተርፕራይዞች፣ ነጋዴዎች፣ የሕብረት ስራ ማህበራትና የተለያዩ አንቀሳቃሾች መሳተፋቸውን ተናግረዋል።


በዚህም ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በስፋት መቅረባቸውን አመላክተዋል።

ሕብረተሰቡም ከእንቁላል ጀምሮ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ የተለያዩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እየሸመቱ መሆኑንም አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026