🔇Unmute
ጂንካ፥ታህሳስ 28/2018(ኢዜአ) :- በጂንካ ከተማ የበዓል ገበያ የዕርድ እንስሳት እና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት አቅርቦትና ዋጋው ተመጣጣኝ መሆኑን ሸማቾች ተናገሩ።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ሸማቾች እንደገለፁት፤ የአትክልት ገበያው ከዚህ ቀደም ከነበረው እጅግ በጣም የቀነሰና የሸማቹን አቅም ያገናዘበ ነው።
በከተማዋ የበዓል ዋዜማ የእንስሳት ገበያውም የተሻለ አቅርቦት እንዳለውና ሁሉም እንደየአቅሙና ፍላጎቱ ለመገበያየት አመቺ መሆኑን ጠቁመዋል።
የከተማዋ ነዋሪ አቶ ዳኜ ገብሬ በበዓል ገበያው የእርድ ከብቶች አቅርቦት ፍላጎትን ያማከለ መሆኑን ገልፀው ሁሉም እንደየአቅሙና ፍላጎቱ ለመገበያየት አመቺ ነው ብለዋል።

አቶ በረከት ገብረማሪያም የተባሉ ነዋሪ በበኩላቸው በዘንድሮ ገበያ በሰንጋ በሬ እና የበግ ሙክት አቅርቦቱ የሚያረካና የሸማቹን አቅምና ፍላጎት ያማከለ መሆኑን ገልጸዋል።
በገበያው በቂ የዶሮ አቅርቦት እንዳለ የጠቆሙት ደግሞ ታዬ አጥናፉ የዕንቁላል ዋጋም ከዚህ ቀደም ከነበረው በቅናሽ እየተሸጠ መሆኑን አመልክተዋል።

በዘንድሮ የበዓል ገበያ ቀይ ሽንኩርት እና ነጭ ሽንኩርት አቅርቦት የተትረፈረፈ በመሆኑ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተሸጠ መሆኑን አስረድተዋል።
በአጠቃላይ በጂንካ ከተማ የበዓል ገበያው የኢዜአ ሪፖርተር ባደረገው ቅኝት የተረጋጋና አቅርቦቱም የሚያረካ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል ።
የጂንካ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሀዝሚ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ምርቶች ከአርሶ አደሮች ሸማቾች ጋር እስኪደርሱ በደላሎች አማካኝነት የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ እንደሚደረግባቸው ገልፀዋል።
እነዚህን ህገወጥ አሰራሮች ለመቅረፍ ፅህፈት ቤቱ ምርቶችን በማህበራትና በኢንተርፕራይዞች አማካኝነት ከአርሶ አደሩ ወደ ሸማቹ በቀጥታ እንዲቀርቡ በሰራው ስራ ያለ አግባብ የሚደረግ የዋጋ ጭማሪን መከላከል መቻሉን ጠቁመዋል ።

በኢንዱስትሪ ምርቶች ላይም በዓልን ምክንያት በማድረግ የሚደረግ ያለ አግባብ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከል በተቋቋመው የቁጥጥርና የክትትል ግብረ ኃይል አማካኝነት ህገወጥነትን የመከላከል ስራ ሲሰራ መቆየቱንም አንስተዋል።
በሌላ በኩል በበዓል ገበያው የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይኖር ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው፥ በበዓል ገበያውም በዕርድ እንስሳት እና በእንስሳት ተዋጽኦ እንዲሁም በቅመማ ቅመም እና በጤፍ ምርት ላይ የአቅርቦት እጥረት አለመኖሩን አብራርተዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025