🔇Unmute
ጂንካ፥ታህሳስ 28/2018(ኢዜአ) :- በጂንካ ከተማ የበዓል ገበያ የዕርድ እንስሳት እና የእንስሳት ተዋጽኦ ምርት አቅርቦትና ዋጋው ተመጣጣኝ መሆኑን ሸማቾች ተናገሩ።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ሸማቾች እንደገለፁት፤ የአትክልት ገበያው ከዚህ ቀደም ከነበረው እጅግ በጣም የቀነሰና የሸማቹን አቅም ያገናዘበ ነው።
በከተማዋ የበዓል ዋዜማ የእንስሳት ገበያውም የተሻለ አቅርቦት እንዳለውና ሁሉም እንደየአቅሙና ፍላጎቱ ለመገበያየት አመቺ መሆኑን ጠቁመዋል።
የከተማዋ ነዋሪ አቶ ዳኜ ገብሬ በበዓል ገበያው የእርድ ከብቶች አቅርቦት ፍላጎትን ያማከለ መሆኑን ገልፀው ሁሉም እንደየአቅሙና ፍላጎቱ ለመገበያየት አመቺ ነው ብለዋል።

አቶ በረከት ገብረማሪያም የተባሉ ነዋሪ በበኩላቸው በዘንድሮ ገበያ በሰንጋ በሬ እና የበግ ሙክት አቅርቦቱ የሚያረካና የሸማቹን አቅምና ፍላጎት ያማከለ መሆኑን ገልጸዋል።
በገበያው በቂ የዶሮ አቅርቦት እንዳለ የጠቆሙት ደግሞ ታዬ አጥናፉ የዕንቁላል ዋጋም ከዚህ ቀደም ከነበረው በቅናሽ እየተሸጠ መሆኑን አመልክተዋል።

በዘንድሮ የበዓል ገበያ ቀይ ሽንኩርት እና ነጭ ሽንኩርት አቅርቦት የተትረፈረፈ በመሆኑ በተመጣጣኝ ዋጋ እየተሸጠ መሆኑን አስረድተዋል።
በአጠቃላይ በጂንካ ከተማ የበዓል ገበያው የኢዜአ ሪፖርተር ባደረገው ቅኝት የተረጋጋና አቅርቦቱም የሚያረካ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል ።
የጂንካ ከተማ አስተዳደር ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ ሀዝሚ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም ምርቶች ከአርሶ አደሮች ሸማቾች ጋር እስኪደርሱ በደላሎች አማካኝነት የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ እንደሚደረግባቸው ገልፀዋል።
እነዚህን ህገወጥ አሰራሮች ለመቅረፍ ፅህፈት ቤቱ ምርቶችን በማህበራትና በኢንተርፕራይዞች አማካኝነት ከአርሶ አደሩ ወደ ሸማቹ በቀጥታ እንዲቀርቡ በሰራው ስራ ያለ አግባብ የሚደረግ የዋጋ ጭማሪን መከላከል መቻሉን ጠቁመዋል ።

በኢንዱስትሪ ምርቶች ላይም በዓልን ምክንያት በማድረግ የሚደረግ ያለ አግባብ የዋጋ ጭማሪን ለመከላከል በተቋቋመው የቁጥጥርና የክትትል ግብረ ኃይል አማካኝነት ህገወጥነትን የመከላከል ስራ ሲሰራ መቆየቱንም አንስተዋል።
በሌላ በኩል በበዓል ገበያው የምርት አቅርቦት እጥረት እንዳይኖር ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው፥ በበዓል ገበያውም በዕርድ እንስሳት እና በእንስሳት ተዋጽኦ እንዲሁም በቅመማ ቅመም እና በጤፍ ምርት ላይ የአቅርቦት እጥረት አለመኖሩን አብራርተዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025