የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በገና በዓል በእርድ እንስሳትና በግብርና ምርት አቅምን ያማከለ አቅርቦት አለ-ሸማቾች

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን/ወልድያ፤ ታህሳስ 28/ 2018 (ኢዜአ)፡- በገና በዓል የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶች አቅርቦት አቅምን ያማከለ መሆኑን የደብረ ብርሃንና ወልድያ ከተሞች ሸማቾች ገለጹ።

የከተማ አስተዳደሮቹ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያዎች በበኩላቸው በቅድመ ዝግጅት ወቅት በተሰራው በርካታ ስራ የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር አስችሏል ብለዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪው አቶ ደመዋዝ አጥላው ለኢዜአ እንደገለጹት ለገና በዓል የእርድ እንስሳት በዋጋም ሆነ በአቅርቦት አማራጭ በመኖሩ በአቅማቸው ለመሸመት ችለዋልⵆ

በዓሉን በለመዱት የመረዳዳትና የተቸገሩ ወገኖችን በመጠየቅ ለማሳለፍ ማቀዳቸውንም ጠቁመዋል።

ሌላዋ ሸማች ወይዘሮ ትርንጎ በየነ በበኩላቸው ለበዓል መዋያ ቅቤ፣ እንቁላል፣ ቀይ ሽንኩርት በተመጣጣኝ ዋጋ መግዛታቸውን ጠቁመዋል።

የገና በዓል የስጦታና የመጠያየቅ በመሆኑ ለበአሉ ከገዙት ላይ በማካፈል በደስታ ለማሳለፍ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል።


የሰሜን ሸዋ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች የግብይት ባለሙያ አቶ ጎበዜ ማርእሸት እንዳሉት ለገና በዓል የእርድ ከብት፣ ዶሮና እንቁላል በተመጣጣኝ ዋጋ በሸማች ማህበራት በኩል ቀርበዋል።

በተያያዘ ዜና በወልድያ ከተማ ለገና በዓል የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸውን ሸማቾች ገልጸዋል።

በከተማዋ በግ ሲገዙ ያገኘናቸው አቶ መዝገቡ አስፋው ለኢዜአ እንዳሉት የበዓል ገበያ አቅርቦቱ የተሻለ መሆኑን አስረድተዋል።

እርሳቸውም የአቅማቸውን በመግዛት ከቤተሰብና ከተቸገሩ ወገኖች ጋር በፍቅር ለማሳላፍ ማቀዳቸውን ገልጸዋል።

ሌላዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ ዘነቡ ተፈራ በበኩላቸው ለበዓሉ የሚያስፈልጋቸውን በአቅማቸው መግዛታቸውንና በዓሉን በደስታ ለማክበር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ከከተማው መደበኛ ገበያዎች በተጨማሪ በጊዜያዊነት ያቋቋማቸው የመገበያያ ቦታዎች ግብይቱ እንዲሳለጥ ምክንያት ሆኗል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025