የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በገና በዓል በእርድ እንስሳትና በግብርና ምርት አቅምን ያማከለ አቅርቦት አለ-ሸማቾች

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን/ወልድያ፤ ታህሳስ 28/ 2018 (ኢዜአ)፡- በገና በዓል የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶች አቅርቦት አቅምን ያማከለ መሆኑን የደብረ ብርሃንና ወልድያ ከተሞች ሸማቾች ገለጹ።

የከተማ አስተዳደሮቹ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያዎች በበኩላቸው በቅድመ ዝግጅት ወቅት በተሰራው በርካታ ስራ የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር አስችሏል ብለዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪው አቶ ደመዋዝ አጥላው ለኢዜአ እንደገለጹት ለገና በዓል የእርድ እንስሳት በዋጋም ሆነ በአቅርቦት አማራጭ በመኖሩ በአቅማቸው ለመሸመት ችለዋልⵆ

በዓሉን በለመዱት የመረዳዳትና የተቸገሩ ወገኖችን በመጠየቅ ለማሳለፍ ማቀዳቸውንም ጠቁመዋል።

ሌላዋ ሸማች ወይዘሮ ትርንጎ በየነ በበኩላቸው ለበዓል መዋያ ቅቤ፣ እንቁላል፣ ቀይ ሽንኩርት በተመጣጣኝ ዋጋ መግዛታቸውን ጠቁመዋል።

የገና በዓል የስጦታና የመጠያየቅ በመሆኑ ለበአሉ ከገዙት ላይ በማካፈል በደስታ ለማሳለፍ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል።


የሰሜን ሸዋ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች የግብይት ባለሙያ አቶ ጎበዜ ማርእሸት እንዳሉት ለገና በዓል የእርድ ከብት፣ ዶሮና እንቁላል በተመጣጣኝ ዋጋ በሸማች ማህበራት በኩል ቀርበዋል።

በተያያዘ ዜና በወልድያ ከተማ ለገና በዓል የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸውን ሸማቾች ገልጸዋል።

በከተማዋ በግ ሲገዙ ያገኘናቸው አቶ መዝገቡ አስፋው ለኢዜአ እንዳሉት የበዓል ገበያ አቅርቦቱ የተሻለ መሆኑን አስረድተዋል።

እርሳቸውም የአቅማቸውን በመግዛት ከቤተሰብና ከተቸገሩ ወገኖች ጋር በፍቅር ለማሳላፍ ማቀዳቸውን ገልጸዋል።

ሌላዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ ዘነቡ ተፈራ በበኩላቸው ለበዓሉ የሚያስፈልጋቸውን በአቅማቸው መግዛታቸውንና በዓሉን በደስታ ለማክበር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ከከተማው መደበኛ ገበያዎች በተጨማሪ በጊዜያዊነት ያቋቋማቸው የመገበያያ ቦታዎች ግብይቱ እንዲሳለጥ ምክንያት ሆኗል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026