የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በገና በዓል በእርድ እንስሳትና በግብርና ምርት አቅምን ያማከለ አቅርቦት አለ-ሸማቾች

Jan 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ብርሃን/ወልድያ፤ ታህሳስ 28/ 2018 (ኢዜአ)፡- በገና በዓል የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶች አቅርቦት አቅምን ያማከለ መሆኑን የደብረ ብርሃንና ወልድያ ከተሞች ሸማቾች ገለጹ።

የከተማ አስተዳደሮቹ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያዎች በበኩላቸው በቅድመ ዝግጅት ወቅት በተሰራው በርካታ ስራ የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር አስችሏል ብለዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪው አቶ ደመዋዝ አጥላው ለኢዜአ እንደገለጹት ለገና በዓል የእርድ እንስሳት በዋጋም ሆነ በአቅርቦት አማራጭ በመኖሩ በአቅማቸው ለመሸመት ችለዋልⵆ

በዓሉን በለመዱት የመረዳዳትና የተቸገሩ ወገኖችን በመጠየቅ ለማሳለፍ ማቀዳቸውንም ጠቁመዋል።

ሌላዋ ሸማች ወይዘሮ ትርንጎ በየነ በበኩላቸው ለበዓል መዋያ ቅቤ፣ እንቁላል፣ ቀይ ሽንኩርት በተመጣጣኝ ዋጋ መግዛታቸውን ጠቁመዋል።

የገና በዓል የስጦታና የመጠያየቅ በመሆኑ ለበአሉ ከገዙት ላይ በማካፈል በደስታ ለማሳለፍ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል።


የሰሜን ሸዋ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶች የግብይት ባለሙያ አቶ ጎበዜ ማርእሸት እንዳሉት ለገና በዓል የእርድ ከብት፣ ዶሮና እንቁላል በተመጣጣኝ ዋጋ በሸማች ማህበራት በኩል ቀርበዋል።

በተያያዘ ዜና በወልድያ ከተማ ለገና በዓል የእርድ እንስሳትና የግብርና ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸውን ሸማቾች ገልጸዋል።

በከተማዋ በግ ሲገዙ ያገኘናቸው አቶ መዝገቡ አስፋው ለኢዜአ እንዳሉት የበዓል ገበያ አቅርቦቱ የተሻለ መሆኑን አስረድተዋል።

እርሳቸውም የአቅማቸውን በመግዛት ከቤተሰብና ከተቸገሩ ወገኖች ጋር በፍቅር ለማሳላፍ ማቀዳቸውን ገልጸዋል።

ሌላዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ ዘነቡ ተፈራ በበኩላቸው ለበዓሉ የሚያስፈልጋቸውን በአቅማቸው መግዛታቸውንና በዓሉን በደስታ ለማክበር መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ከከተማው መደበኛ ገበያዎች በተጨማሪ በጊዜያዊነት ያቋቋማቸው የመገበያያ ቦታዎች ግብይቱ እንዲሳለጥ ምክንያት ሆኗል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026