የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በከተማው ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች የዲጂታል እውቀት የማሳደግ ስራ ይከናወናል

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ጥር 3/2018(ኢዜአ)፡- በስራ ፈጠራ የሚሰማሩ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ለማጎልበት እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጎንደር ከተማ አስተዳደር አስታወቀ።

የጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና "ኦርቢት ኢኖቬሽን ሀብ" የተባለ ድርጅት በጋራ በመሆን በስራ ፈጠራ ክህሎት ላሰለጠኗቸው 45 ወጣቶች ዛሬ የማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ ደብሬ የኋላ ለሰልጣኞቹ እንደገለጹት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን ለማሳካት ልዩ የስራ ፈጠራ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች ተሳትፎ ማሳደግ ይገባል።


የከተማ አስተዳደሩ ልዩ የስራ ፈጠራ ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች ተቋማዊ የአሰራር ስርአቶችን በመዘርጋት ውጤታማና እንዲሆኑ ሁለተናዊ ድጋፍ በማድረግ ሃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል፡፡

የዲጂታል ቴክኖሎጂ በሀገራችን ለተዘመገቡ ኢኮኖሚያዊ እድገቶች አዎንታዊ ሚና እንደነበረው ጠቁመው የሰራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በከተማው በማደራጀት ተሰጥዋቸውን ለሀገር ልማትና እድገት የሚያውሉበት ምቹ አውድ እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡

የጎንደር ከተማ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተስፋሁን መኮንን እንደገለጹት የስራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ወጣቶች የዲጂታል ክህሎትና እውቀታቸው እንዲዳብር ኮሌጁ ተገቢውን የሙያ ስልጠና እንዲያገኙ እያደረገ ይገኛል፡፡

የስራ ፈጠራ ሃሳብ ተወዳዳሪነትን፣ ብቃትንና ዘመኑን የዋጀ መሆን እንዳለበት ጠቁመው ለስልጠናው የተመረጡ ወጣቶችም መስፈርቱን ያሟሉ እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡


"የኦርቢት ኢኖቬሽን ሀብ" የኮሚኒቲ ዴቨሎፕመንት ፕሮግራም ማኔጀር ቅኔል ሃይሉ በበኩላቸው በሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች የስራ ፈጣሪ ወጣቶችን ራእይ ለማሳካት የዲጂታል ክህሎት ስልጠና የሚያገኙበት አሰራርን በመዘርጋት አየተተገበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ድርጅቱ ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር በመተባበር በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በትግራይና በደቡብ ክልሎቸ በ6 ዙር የስራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በማወዳደር የቴክኖሎጂ ስልጠና እንዲያገኙ እየደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በጎንደር ከተማም 218 የስራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በማወዳደር ከዚህ ውስጥ መመዘኛውን ያለፉ 45 ወጣቶች ለሶስት ተከታታይ ወራት የንድፈ ሃሳብና የተግባር ስልጠና በመስጠት ወደ ስራ የሚገቡበትን ሁኔታ ማመቻቸቱን አስረድተዋል፡፡

ከሰልጣኞቹ መካከል የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር አዲሱ ወርቄ ስልጠናው በዲጂታል አለም ውስጥ የስራ ፈጠራ ሃሳቦቻችንን አንዴት ማሳካት እንደምንችል እውቀትና ክህሎት መጨበጥ እንድንችል አግዞናል ብለዋል፡፡

የሳይካትሪስት ባለሙያ የሆነችው ቤተልሄም ጌታቸው በበኩሏ የስራ ፈጠራ ሃሳቦቼን እንዴት ወደ መሬት ማውረድና ገበያ ላይ ማውጣት አንደምችል ስልጠናው የተሟላ እውቀትና ግንዛቤ ፈጥሮልኛል ብላለች።

በስነ ስርአቱ ላይ የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችን ጨምሮ ስልጠናውን የተከታተሉ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች ተሳታፊ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025