🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦የተቋማት ግንባታ እና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል የተሰናዳው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ ተሳትፈዋል።
በዚህም ኮንፈረንሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም ጉዞን መለስ ብሎ ለመገምገም እና የመጪውን ጊዜ የቅድሚያ ምልከታ ለማስቀመጥ የረዳ ጠቃሚ መድረክ እንደነበር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል።

የተቋማት ግንባታ እና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ብለዋል።።
በፊስካል አስተዳደር፣ በሞኒተሪ እና ፋይናንስ ዘርፍ ሪፎርም በገቢ አስተዳደር፣ በካፒታል ገበያ አስተዳደር፣ በኢንቨስትመንት አስተዳደር እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ሪፎርም ያሳካናቸውን ድሎች ለማጤን ያገዘ እና የሪፎርሞቹን ጉዞ ፍጥነት አጥብቆ በመያዝ የመራመድን እና ሰፊውን የኢኮኖሚ ሽግግር አጀንዳ የማላቅን አስፈላጊነት ለመገንዘብ የረዳ መድረክ ነበር ሲሉም ነው የገለጹት።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025