🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦የተቋማት ግንባታ እና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል የተሰናዳው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ ተሳትፈዋል።
በዚህም ኮንፈረንሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም ጉዞን መለስ ብሎ ለመገምገም እና የመጪውን ጊዜ የቅድሚያ ምልከታ ለማስቀመጥ የረዳ ጠቃሚ መድረክ እንደነበር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል።

የተቋማት ግንባታ እና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ብለዋል።።
በፊስካል አስተዳደር፣ በሞኒተሪ እና ፋይናንስ ዘርፍ ሪፎርም በገቢ አስተዳደር፣ በካፒታል ገበያ አስተዳደር፣ በኢንቨስትመንት አስተዳደር እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ሪፎርም ያሳካናቸውን ድሎች ለማጤን ያገዘ እና የሪፎርሞቹን ጉዞ ፍጥነት አጥብቆ በመያዝ የመራመድን እና ሰፊውን የኢኮኖሚ ሽግግር አጀንዳ የማላቅን አስፈላጊነት ለመገንዘብ የረዳ መድረክ ነበር ሲሉም ነው የገለጹት።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025