🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 7/2018(ኢዜአ)፦የተቋማት ግንባታ እና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል የተሰናዳው የዐበይት ተቋማት አፈፃፀም ግምገማ ኮንፈረንስ ላይ ተሳትፈዋል።
በዚህም ኮንፈረንሱ የኢኮኖሚ ሪፎርም ጉዞን መለስ ብሎ ለመገምገም እና የመጪውን ጊዜ የቅድሚያ ምልከታ ለማስቀመጥ የረዳ ጠቃሚ መድረክ እንደነበር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል።

የተቋማት ግንባታ እና ዝግጁነትን ማረጋገጥ የመንግሥት ዐበይት ኃላፊነቶች ናቸው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ በዚህ የተነሳ ነው የሀገራችንን የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ዘርፍ ለማጠናከር የታሰበባቸው ሰፋፊ እርምጃዎችን የወሰድነው ብለዋል።።
በፊስካል አስተዳደር፣ በሞኒተሪ እና ፋይናንስ ዘርፍ ሪፎርም በገቢ አስተዳደር፣ በካፒታል ገበያ አስተዳደር፣ በኢንቨስትመንት አስተዳደር እና የመንግሥት የልማት ድርጅቶች አስተዳደር ሪፎርም ያሳካናቸውን ድሎች ለማጤን ያገዘ እና የሪፎርሞቹን ጉዞ ፍጥነት አጥብቆ በመያዝ የመራመድን እና ሰፊውን የኢኮኖሚ ሽግግር አጀንዳ የማላቅን አስፈላጊነት ለመገንዘብ የረዳ መድረክ ነበር ሲሉም ነው የገለጹት።
ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...
Jun 6, 2026
ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...
May 26, 2026
ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...
May 21, 2026
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026