🔇Unmute
ባህር ዳር፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በከተሞችም ይሁን በገጠር የልማት ተደራሽነትን በማስፋት ፍትሃዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች የልማት ተደራሽነትን በማስፋት ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥና የጋራ ብልጽግናን እውን የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ከከተሞች በተጨማሪ ለገጠር አካባቢዎችም ተመሳሳይ ትኩረት በማድረግ የህብረተሰቡን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ለዚህ የልማት እቅድ መሳካትም ከመንግስት ጥረት በተጨማሪ ባለሃብቶች፣ አጋር ተቋማትና አጠቃላይ የህብረተሰቡ ትብብርና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

የክልሉ መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ቢሮ ሃላፊ ጋሻው አወቀ (ዶ/ር)፤ የገጠር ልማትን ለማሳካትና የመንገድ ተደራሽነትን ለማስፋት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ ዘመናዊና ስማርት ከተሞችን እውን የማድረግ እና የገጠር ቀበሌዎችን በመንገድ በማስተሳሰርና የገጠር ኮሪደር ልማትን ለማሳካት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑም አንስተዋል።
በዚህም በክልሉ እስካሁን ከ2 ሺህ 664 በላይ የገጠር ቀበሌዎችን በመንገድ ማስተሳሰር መቻሉን ተናግረዋል።
በቀጣይም በገጠር ከመንገድ መሰረተ ልማት ባሻገር ሌሎች ተያያዥ መሰረተ ልማቶች የሚከናወኑ መሆኑን አንስተው የኮሪደር ልማቱ በተመረጡ አካባቢዎች በመጀመር የሚሰፋ ይሆናል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025