የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ፍትሃዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል 

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በከተሞችም ይሁን በገጠር የልማት ተደራሽነትን በማስፋት ፍትሃዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች የልማት ተደራሽነትን በማስፋት ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥና የጋራ ብልጽግናን እውን የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ከከተሞች በተጨማሪ ለገጠር አካባቢዎችም ተመሳሳይ ትኩረት በማድረግ የህብረተሰቡን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

ለዚህ የልማት እቅድ መሳካትም ከመንግስት ጥረት በተጨማሪ ባለሃብቶች፣ አጋር ተቋማትና አጠቃላይ የህብረተሰቡ ትብብርና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።


የክልሉ መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ቢሮ ሃላፊ ጋሻው አወቀ (ዶ/ር)፤ የገጠር ልማትን ለማሳካትና የመንገድ ተደራሽነትን ለማስፋት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ ዘመናዊና ስማርት ከተሞችን እውን የማድረግ እና የገጠር ቀበሌዎችን በመንገድ በማስተሳሰርና የገጠር ኮሪደር ልማትን ለማሳካት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑም አንስተዋል።

በዚህም በክልሉ እስካሁን ከ2 ሺህ 664 በላይ የገጠር ቀበሌዎችን በመንገድ ማስተሳሰር መቻሉን ተናግረዋል።

በቀጣይም በገጠር ከመንገድ መሰረተ ልማት ባሻገር ሌሎች ተያያዥ መሰረተ ልማቶች የሚከናወኑ መሆኑን አንስተው የኮሪደር ልማቱ በተመረጡ አካባቢዎች በመጀመር የሚሰፋ ይሆናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026