የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሉ ፍትሃዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል 

Jan 16, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ ጥር 8/2018 (ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በከተሞችም ይሁን በገጠር የልማት ተደራሽነትን በማስፋት ፍትሃዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ አሕመዲን መሀመድ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች የልማት ተደራሽነትን በማስፋት ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን የማረጋገጥና የጋራ ብልጽግናን እውን የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ከከተሞች በተጨማሪ ለገጠር አካባቢዎችም ተመሳሳይ ትኩረት በማድረግ የህብረተሰቡን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

ለዚህ የልማት እቅድ መሳካትም ከመንግስት ጥረት በተጨማሪ ባለሃብቶች፣ አጋር ተቋማትና አጠቃላይ የህብረተሰቡ ትብብርና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።


የክልሉ መንገድ፣ ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ቢሮ ሃላፊ ጋሻው አወቀ (ዶ/ር)፤ የገጠር ልማትን ለማሳካትና የመንገድ ተደራሽነትን ለማስፋት የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ ዘመናዊና ስማርት ከተሞችን እውን የማድረግ እና የገጠር ቀበሌዎችን በመንገድ በማስተሳሰርና የገጠር ኮሪደር ልማትን ለማሳካት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑም አንስተዋል።

በዚህም በክልሉ እስካሁን ከ2 ሺህ 664 በላይ የገጠር ቀበሌዎችን በመንገድ ማስተሳሰር መቻሉን ተናግረዋል።

በቀጣይም በገጠር ከመንገድ መሰረተ ልማት ባሻገር ሌሎች ተያያዥ መሰረተ ልማቶች የሚከናወኑ መሆኑን አንስተው የኮሪደር ልማቱ በተመረጡ አካባቢዎች በመጀመር የሚሰፋ ይሆናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025