የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የአዲስ አበባን የስማርት ሲቲ ግንባታ ይበልጥ የሚያፋጥን ነው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ)፦ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የአዲስ አበባን የስማርት ሲቲ ግንባታ ይበልጥ የሚያፋጥን መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትግበራን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት፤ዲጂታል 2030 ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን መገንባት ቁልፍ የስትራቴጂው ግቦች እንደሆኑ አስረድተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ‎ምክትል ኃላፊ ቱሉ ጥላሁን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በመዲናዋ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ የሆኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች በስኬት ተከናውነዋል።

በተለይም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በከተማዋ ውጤታማ አፈጻጸም እንደተመዘገበበት ጠቅሰው፤ ይህም ለዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ሽግግር አስተማማኝ መሠረት መጣሉን አስታውቀዋል።

በመዲናዋ በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ የአይሲቲ ፓርክ መጠናከርን ለአብነት አንስተዋል።

‎ቀደም ሲል በዝቅተኛ ፍጥነትና በወረዳ ደረጃ ተወስኖ የነበረው የኔትወርክ ትስስር መሻሻሉን የገለጹት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ በአሁኑ ወቅት ሰማንያ ስድስት የመንግሥት ተቋማት በሲቲ ኔት (City Net) መሠረተ ልማት መገናኘታቸውን አስታውቀዋል።

‎በተጨማሪም በከተማዋ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ተደራሽነት የስትራቴጂው ውጤት መሆናቸውን አንስተዋል፡፡

በከተማዋ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ በማድረግ ዜጎች ባሉበት ሆነው ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ መሰረት መጣሉን ገልጸዋል።

‎ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የአዲስ አበባን የስማርት ሲቲ ግንባታ ይበልጥ የሚያፋጥንና የዜጎችን ሕይወት የሚያቀል መሆኑን ተናግረዋል፡፡፡

‎ስትራቴጂው ዜጎች የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ሳይሆኑ፣ አዳዲስ የዲጂታል መፍትሔዎችን የሚያመነጩ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርም አመልክተዋል።

‎በአጠቃላይ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አዲስ አበባን ዘመናዊና የበለጸገች ስማርት ሲቲ የማድረግ ራዕይን እውን እንደሚያደርግ አስታውቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025