🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥር 12/2018(ኢዜአ)፦ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የአዲስ አበባን የስማርት ሲቲ ግንባታ ይበልጥ የሚያፋጥን መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትግበራን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት፤ዲጂታል 2030 ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን መገንባት ቁልፍ የስትራቴጂው ግቦች እንደሆኑ አስረድተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ቱሉ ጥላሁን (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በመዲናዋ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ የሆኑ የመሠረተ ልማት ሥራዎች በስኬት ተከናውነዋል።
በተለይም ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ በከተማዋ ውጤታማ አፈጻጸም እንደተመዘገበበት ጠቅሰው፤ ይህም ለዲጂታል 2030 ስትራቴጂ ሽግግር አስተማማኝ መሠረት መጣሉን አስታውቀዋል።
በመዲናዋ በዲጂታል 2025 ስትራቴጂ የአይሲቲ ፓርክ መጠናከርን ለአብነት አንስተዋል።
ቀደም ሲል በዝቅተኛ ፍጥነትና በወረዳ ደረጃ ተወስኖ የነበረው የኔትወርክ ትስስር መሻሻሉን የገለጹት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ በአሁኑ ወቅት ሰማንያ ስድስት የመንግሥት ተቋማት በሲቲ ኔት (City Net) መሠረተ ልማት መገናኘታቸውን አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በከተማዋ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ተደራሽነት የስትራቴጂው ውጤት መሆናቸውን አንስተዋል፡፡
በከተማዋ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ በማድረግ ዜጎች ባሉበት ሆነው ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ መሰረት መጣሉን ገልጸዋል።
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የአዲስ አበባን የስማርት ሲቲ ግንባታ ይበልጥ የሚያፋጥንና የዜጎችን ሕይወት የሚያቀል መሆኑን ተናግረዋል፡፡፡
ስትራቴጂው ዜጎች የቴክኖሎጂ ተጠቃሚ ብቻ ሳይሆኑ፣ አዳዲስ የዲጂታል መፍትሔዎችን የሚያመነጩ ፈጣሪዎች እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርም አመልክተዋል።
በአጠቃላይ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አዲስ አበባን ዘመናዊና የበለጸገች ስማርት ሲቲ የማድረግ ራዕይን እውን እንደሚያደርግ አስታውቀዋል፡፡
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026