የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢትዮጵያ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮች ተግባራዊ እያደረገች ነው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥር 14/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ በቴክኖሎጂ የታገዙ አሰራሮች ተግባራዊ እያደረገች መሆኑን ተገለጸ።

የኢትዮጵያ ንብ ሀብት ማህበር እና የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት(UNIDO) በንብ ሀብትና በማር ምርታማነት ዙሪያ የመከሩበት የውይይት መድረክ ተካሂዷል።


በመድረኩ የተገኙት የግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና አሳ ሀብት ዘርፍ የሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ ግርማ ሙሉጌታ እንደተናገሩት፤ የማር ሀብትን በውጤታማነት ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችል የተሻሻለ አሰራር ተግባራዊ ተደርጓል።

መንግስት ለግብርናው ዘርፍ የሰጠው ልዩ ትኩረት መነቃቃት መፍጠሩን ገልጸው፤ አምራቾች በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራርን እንዲከተሉ ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን ጠቁመዋል።

ለዚህም ስኬት ከበለጸጉ ሀገራት ጋር የሚደረግ የቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር፣ የልምድ ልውውጥ ስራዎች እንዲሁም የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ተሳትፎ ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አብራርተዋል።

መድረኩ የማር ምርት ጥራትን በመጠበቅ ለውጭ ገበያ የሚቀርበውን ምርት ለማሳደግና ዘላቂ የገበያ ትስስር ለመፍጠር ያለመ መሆኑም ጠቁመዋል።


በአፍሪካ ህብረት እና በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት(UNIDO) ተጠሪ ስቴፍን ካግቦ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ እያስመዘገበች ያለው እድገት የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምሮ ለማቅረብ የተገነቡት ሶስት የተቀናጁ የግብርና ምርት ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዘርፉ ትልቅ ተስፋ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

እነዚህ ፓርኮች ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የፈሰሰባቸውና ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል የፈጠሩ መሆናቸውን ጠቁመው፤ የውጭ ኢንቨስትመንት ፍሰትን በመሳብ በኩል ውጤታማ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በዘርፉ ስኬታማ ለመሆን ለሚፈልጉ ሌሎች ሀገራት እንደ ትልቅ የልምድ ምንጭ እያገለገሉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ኢትዮጵያ በማር ምርት ዘርፍ የጀመረቻቸው ስራዎች ውጤታማ እንደሚሆኑ ያላቸውን እምነት ገልጸው፤ የUNIDO እና የኢትዮጵያ መንግስት ቅንጅት ለሌሎች ሀገራትም አርአያ የሚሆን ተግባር ነው ብለዋል፡፡


የኢትዮጵያ ንብ ሀብት ማህበር ዋና ስራ አስኪያጅ ነጋሽ በቃና በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ማርን እሴት ጨምሮ ለውጭ ገበያ በማቅረብ በኩል መንግስት ለዘርፉ ምርታማነት ያመቻቸውን የፖሊሲና የአሰራር ድጋፎች በአግባቡ ለመጠቀም ዝግጁ መሆናቸውን አመላክተዋል።

ማህበሩ በመንግስትና በግል አጋርነት የሚከናወኑ ተግባራት እንዲጠናከሩ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ ውይይቱ ለሀገሪቱ የማር ዘርፍ እድገት አዲስ አቅጣጫ ይጠቁማል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026