የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍቱ ለሀገር-አቀፍ ፈተናው የተሻለ ዝግጅት ለማድረግና የላቀ ውጤት ለማምጣት ያግዛል

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰቆጣ ፤የካቲት 3/2018(ኢዜአ)፡-ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍቱ ለሀገር-አቀፍ ፈተናው የተሻለ ዝግጅት ለማድረግና የላቀ ውጤት ለማምጣት የሚያግዝ መሆኑን የሰቆጣ ከተማ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ገለጹ።

የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ በሰቆጣ ያስገነባው ''ሰላም የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ ሰማዕታት መታሰቢያ ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት'' ትናንት መመረቁ ይታወሳል።


ኢዜአ ያነጋገራቸው የሰቆጣ ከተማ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍቱ ግንባታ የበለጠ እንዲያነቡና ተጨማሪ ዕውቀት እንዲታጠቁ የሚያነሳሳ መሆኑን ተናግረዋል።

የ12ኛ ክፍል ተማሪው ሳህለጊዮርጊስ ደባሹ በከተማዋ ደረጃውን የጠበቀ ቤተ-መጻሕፍት ባለመኖሩ በክፍል ከሚሰጣቸው ትምህርት ውጭ ተጨማሪ መጽሐፍት ለማግኘት ይቸገሩ እንደነበር አስታውሷል።


የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት ለአገልግሎት መብቃት ዘመኑ የሚጠይቀውን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዕውቀት እንዲገበዩና ብቁና ተወዳዳሪ ለመሆን ያስችላል ነው ያለው።

ዘንድሮ ለሚወስደው ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና የተሻለ ዝግጅት ለማድረግና የላቀ ውጤት ለማምጣትም የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍቱ ግንባታ ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጿል።


ተማሪ እሌኒ ቢምረውና ተማሪ አዱኛ ንጉሴ በበኩላቸው ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍቱ የሚፈልጉትን መጽሐፍት በቀላሉ በማግኘት ራሳቸውን እንዲያበቁ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።

ከመደበኛ ትምህርት ባለፈ ለጠቅላላ ዕውቀት የሚሆኑ አባሪ መጽሐፍትን በማንበብ የዕውቀት አድማስንና እይታን ለማስፋት ወሳኝ መሆኑንም አመልክተዋል።


የዋግ ስዩም አድማሱ ወሰን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ግርማ መክብብ እንዳሉት የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍቱ ለተማሪዎች ውጤት መሻሻል ትልቅ አስተዋፅኦ አለው።

ተማሪዎች አስፈላጊውን አጋዥ መጽሐፍት በቀላሉ እንዲያገኙ ከማስቻሉም ባለፈ ሀገር አቀፍ ፈተናውን በብቃት እንዲወጡና የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ የሚያግዝ መሆኑን አመልክተዋል።


የዳሎል ማዕከላዊ ዕዝ የሰራዊት አባላት በ70 ሚሊዮን ብር በሰቆጣ ከተማ ያስገነቡት የዲጂታል ቤተ-መጻሕፍትን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በይፋ መመረቃቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026