የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የተደረገልን የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ለተሻለ ሥራ የሚያነሳሳን ነው - አርሶ አደሮች 

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሮቤ ፤ የካቲት 5/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን የተደረገላቸው የኢንቨስትመንት ማበረታቻ ለተሻለ ሥራ እንደሚያነሳሳቸው ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት በመሸጋገር እውቅና ያገኙ አርሶ አደሮች ገለጹ።

በባሌ ዞን ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት ለተሸጋገሩ 301 አርሶ አደሮች እና ማህበራት የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱንም የዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ገልጿል።


አርሶ አደር ኡመር አህመድ ባለፉት ዓመታት በተሰማሩበት የግብርና መስክ ውጤታማ በመሆን ወደ ኢንቨስትመንት ከተሸጋገሩ አርሶ አደሮች መካከል አንዱ ናቸው፡፡


አርሶ አደሩ በስንዴና ሌሎች ሰብሎች ሽያጭ ውጤታማ በመሆን 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር አስመዝግበው በዛሬው እለት ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን ነው የሚገልጹት።

በአሁኑ ወቅትም በግብርና የኢንቨስትመንት አማራጮች ለመሰማራት ሶስት ሄክታር የኢንቨስትመንት መሬትን በማበረታቻነት ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

በተሰማሩበት የአትክልትና ፍራፍሬ ልማትና ሽያጭ ስራ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸውን የገለጹት ደግሞ የደሎ መና ወረዳ አርሶ አደር አብዱልከሪም ኢብራሂም ናቸው።


በአሁኑ ወቅት ከተሰጣቸው የእውቅና ሰርተፊኬት ባሻገር በኢንቨስትመንት ማበረታቻነት 10 ሄክታር የመሥሪያ ቦታ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

አርሶ አደሮቹ እንዳሉት የተደረገላቸው ዕውቅናና የኢንቨስትመንት ማበረታቻ መሬት በቀጣይ የተሻለ ሥራ ለመሥራት የሚያነሳሳ ነው ይላሉ።

የዞኑ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ መሐመድ ኢብሮ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ በዞኑ 301 አርሶ አደሮች እና የጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት ከግብርና ወደ ኢንቨስትመንት ተሸጋግረዋል።


አርሶ አደሮቹና ኢንተርፕራይዞቹ ባለፉት ዓመታት በተሰማሩበት የሥራ መስክ ውጤታማ ከመሆን ባሻገር በነፍስ ወከፍ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ለማስመዝገብ እንደቻሉም ተናግረዋል።

ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩት አርሶ አደሮች ወደ ሥራ ሲገቡ ከ14 ሺህ 400 ለሚበልጡ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል ይፈጥራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክተዋል።

ወደ ኢንቨስትመንት ለተሸጋገሩ አርሶ አደሮች ከ1 ሺህ 202 ሄክታር የሚበልጥ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ የተሰጣቸው መሆኑን ነው ኃላፊው የተናገሩት።

ለአርሶ አደሮቹና ማህበራቱ በተሰማሩበት ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ የመሬት አቅርቦትና ሌሎች ማበረታቻዎች እንደተደረገላቸው የገለጹት ደግሞ የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አብርሃም ኃይሌ ናቸው።


ባለፉት ዓመታት በግብርናው ዘርፍ ባከናወኑት ውጤታማ ሥራ ወደ ኢንቨስትመንት የተሸጋገሩት ግንባር ቀደም አርሶ አደሮች የግብርናው መስክ ሽግግር አዎንታዊ ማሳያዎች መሆናቸውን አክለዋል።

በዞኑ በተያዘው በጀት ዓመት የዛሬዎቹን ጨምሮ ከ437 የሚበልጡ ግንባር ቀደም አርሶ አደሮችና ማህበራት ባስመዘገቡት ከ1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ካፒታል ወደ ኢንቨስትመንት መሸጋገራቸው ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025