የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የሁለተኛ ቀን ውሎ

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በህብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።

“ዘላቂ የውኃ አቅርቦትና ደኅንነቱ የተጠበቀ የንጽህና አጠባበቅ ሥርዓቶችን ማረጋገጥ፤ ለአጀንዳ 2063 ግቦች ስኬታማነት” የጉባኤው መሪ ቃል ነው።

ትናንት የተጀመረው ጉባኤ ዛሬም በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ መምከሩን ይቀጥላል።

ከመሪ ቃሉ ጋር በተያያዘ ዘላቂ የውሃ አቅርቦትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የንጽህና አጠባበቅ ስርዓት፣ አካታች እድገት፣ ጤናማ ማህበረሰብና ጠንካራ ስነ ምህዳር መገንባት፣ የተፈጥሮ ሀብት ዘላቂ አጠቃቀምና የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ጉዳዮች ውይይት ይደረግባቸዋል።

ውሃ እና ንጽህና የአጀንዳ 2063 አጀንዳን ከማሳካት አንጻር ያላቸው ሚና ይቃኛል።

ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ የሰው ኃይል ልማት፣ ተቋማዊ እና የፋይናንስ ሪፎርሞች፣ ቀጣናዊ አጋርነትና አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላት ሚና ጉባኤው ከሚመክርባቸው አጀንዳዎች መካከል ይጠቀሳሉ።

የአፍሪካ ህብረት የ2026 መሪ ሀሳብ ይፋ ማድረጊያ መርሐ-ግብርም ዛሬ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ይገኝበታል። በመርሐ-ግብሩ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አመራሮች እና የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ይገኛሉ።


የሀገራት መሪዎች የሚገኙበት የአፍሪካ ሀገራት የውሃ ኢንቨስትመንት እና ፋይናንስ የተመለከተ ከፍተኛ መድረክም ይካሄዳል።

የአፍሪካ ህብረት የደቡብ ሱዳን የከፍተኛ ባለስልጠናት ኮሚቴ በደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ምክክር ያደርጋል።

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የሚገኙ የአፍሪካ አባል ሀገራት (A3) የሚኒስትሮች ስብሰባም ይከናወናል።

ሱማሊያ፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ላይቤሪያ የምክር ቤቱ የአፍሪካ አባል ናቸው።

የዓለም የጤና ስርዓት ምህዳርን ማሻሻል ላይ የዓለም ትብብር ምን መምሰል እንዳለበት የሚመክር ጉባኤም ይካሄዳል።

የአፍሪካ ህብረት የፖለቲካ ጉዳዮች፣ የሰላም እና ደህንነት ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሌ አዶዬ በአህጉሪቱ የሰላም እና ጸጥታ ሁኔታ ላይ መግለጫ ይሰጣሉ።

በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ የጎንዮሽ ሁነቶችም እንዲሁ ከዛሬ መርሃ ግብሮች መካከል ናቸው።

የተለያዩ የአፍሪካ ህብረት ተቋማት እና አደረጃጀቶች በስራዎቻቸው ዙሪያ መግለጫዎች እንደሚሰጡና በአህጉራዊ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ ውይይቶች እንደሚካሄዱ የወጣው መርሃ ግብር ያሳያል።

39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ዛሬ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026