የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

የገጠር መሬትን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር አርሶአደሩ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ ነው

Mar 4, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ የካቲት 18/2018(ኢዜአ)፦ የገጠር መሬትን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር አርሶአደሩየኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መሬትና ህብረት ስራ ማደራጃ ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር "ብሔራዊ መታወቂያ ለገጠር መሬት ባለይዞታዎች" በሚል መሪ ሃሳብ የምክክር መድረክ አካሂዷል።


በግብርና ሚኒስቴር የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ትዕግስቱ ገብረመስቀል እንደገለፁት፤ የገጠር መሬትን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር የአርሶ አደሩን ዘላቂ የመሬት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እና ብልሹ አሰራርን ማስቀረት ይቻላል።

አርሶ አደሩ ማሳውን አስይዞ የብድር አገልግሎት እንዲያገኝ በማድረግ ምርትና ምርታማነቱን ለማሳደግ እንዲችልም የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ካሉት ከ50 ሚሊዮን በላይ የአርሶ አደር ማሳዎች መካከል 32 ሚሊዮን ለሚሆኑት የባለቤትነት ይዞታ መሰራቱን ለአብነት አንስተዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ በበኩላቸው፤ የገጠር መሬትን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር የማስተሳሰሩ ሂደት አርሶ አደሩን በተሻለ መልኩ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው ብለዋል።


ይህም በሀገር አቀፍ ደረጃ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመተግበር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር እንደሆነም አስረድተዋል።

ትግበራው የመሬት አስተዳደርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ እንዲካሔድ በማድረግ አለመግባባቶችን ለመፍታት የሚያስችል ሲሆን መሬትን ለተፈለገው አገልግሎት ለመጠቀም ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ጠቅሰዋል።

የክልሉ መሬትና ህብረት ሥራ ማደራጃ ቢሮ ኃላፊ አቶ ካሚል ሀሚድ በበኩላቸው፤ ‎በክልሉ ለ277 ሺህ 274 ማሳዎች ቋሚ የይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሠጠቱን ነው የተናገሩት።


‎አርሶ አደሩ የመሬት ባለቤትነት መብቱን በመጠቀም ማሳውን በማልማት፣ በማከራየት እንዲሁም ከባንክ ጋር በማስተሳሰር የብድር አቅርቦት ማግኘት እንደሚችል ጠቁመዋል።

በመድረኩ ላይ የፌዴራል፣ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እና የዘርፉ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በግብርናው ዘርፍ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎች ይጠናከራሉ

ዱራሜ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርና ዘርፍ ያሉ ፀጋዎችን ለልማት በማዋል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተጀመሩ ሥ...

Jun 6, 2026

የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ ነው

ደሎ መና፤ ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የአርብቶ አደሩን የድርቅ ተጋላጭነት ለመቀነስ የሚያግዙ ዘመናዊ የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑ...

May 26, 2026

ክልሉን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም ይገባል

ጋቼኖ ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን የሰላም፣ የልማትና የመቻቻል ተምሳሌት ለማድረግ የህዝቡን አቅም አቀናጅቶ መጠቀም እንደሚገባ የክ...

May 21, 2026

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026