🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ 4ኛው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የኢንቨስትመንት ፎረም መጋቢት 17 እና 18 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
ፎረሙን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የዓለም ባንክ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ፎረሙ በኮሚሽኑ፣ በገንዘብ ሚኒስቴርና በአጋር የልማት ድርጅቶች ትብብር የተዘጋጀ ነው።
የመድረኩ ዋና ዓላማ አዳዲስ የውጭና የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ፣ መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳየት እንዲሁም በቅርቡ የተደረጉ አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ለባለሀብቶች ማስተዋወቅ ነው ብለዋል።
በፎረሙ ዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ አማካሪዎችና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል፡፡
መገናኛ ብዙኃን የሀገሪቱን የኢንቨስትመንት ዕድሎች በማስተዋወቅና የፎረሙን ስኬት በማብሰር በኩል የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ ኃላፊነት እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በበኩላቸው፤ መንግስት ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ሰፊ የፖሊሲና የሕግ ማዕቀፍ ማሻሻያዎችን ማድረጉን ገልጸዋል።
በሀገሪቱ ባሉ እምቅ አቅሞችና በመንግስት የሪፎርም ስራዎች ምክንያት በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ከፍተኛ መነሳሳት መኖሩን ተናግረዋል፡፡
ይህ ፎረም በእነዚህ ዕድሎች ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ትልቅ መድረክ እንደሚሆንም አስረድተዋል።
በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ የደቡብ ሱዳንና ሱዳን ዳይሬክተር ሜርየም ሳሊም እንዳሉትም፤ ኢትዮጵያ ያላትን ከፍተኛ አቅም በመጥቀስ በፎረሙ ለመሳተፍ አሁን ትክክለኛው ጊዜ ነው ብለዋል።
ወጣትና እያደገ ያለ የሰው ኃይል መኖሩ፣ ስትራቴጂካዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ፣ ጠንካራ የግብርና መሠረትና እየሰፋ ያለ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ዳይሬክተሯ ለኢትዮጵያ ተመራጭነት እንደ ምክንያት ጠቅሰዋል፡፡
በተጨማሪም ኢትዮጵያ በተስፋ ብቻ ሳትወሰን በተግባር የሚታዩ የሪፎርም እርምጃዎችን እየወሰደች በመሆኗ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025