🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ የካቲት 24/2018(ኢዜአ)፦ 4ኛው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የኢንቨስትመንት ፎረም መጋቢት 17 እና 18 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
ፎረሙን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የዓለም ባንክ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ፎረሙ በኮሚሽኑ፣ በገንዘብ ሚኒስቴርና በአጋር የልማት ድርጅቶች ትብብር የተዘጋጀ ነው።
የመድረኩ ዋና ዓላማ አዳዲስ የውጭና የሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ፣ መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳየት እንዲሁም በቅርቡ የተደረጉ አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ለባለሀብቶች ማስተዋወቅ ነው ብለዋል።
በፎረሙ ዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች፣ የንግዱ ማህበረሰብ መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ አማካሪዎችና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል፡፡
መገናኛ ብዙኃን የሀገሪቱን የኢንቨስትመንት ዕድሎች በማስተዋወቅና የፎረሙን ስኬት በማብሰር በኩል የሚጠበቅባቸውን ሙያዊ ኃላፊነት እንዲወጡም ጥሪ አቅርበዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በበኩላቸው፤ መንግስት ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ሰፊ የፖሊሲና የሕግ ማዕቀፍ ማሻሻያዎችን ማድረጉን ገልጸዋል።
በሀገሪቱ ባሉ እምቅ አቅሞችና በመንግስት የሪፎርም ስራዎች ምክንያት በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ከፍተኛ መነሳሳት መኖሩን ተናግረዋል፡፡
ይህ ፎረም በእነዚህ ዕድሎች ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ትልቅ መድረክ እንደሚሆንም አስረድተዋል።
በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ የደቡብ ሱዳንና ሱዳን ዳይሬክተር ሜርየም ሳሊም እንዳሉትም፤ ኢትዮጵያ ያላትን ከፍተኛ አቅም በመጥቀስ በፎረሙ ለመሳተፍ አሁን ትክክለኛው ጊዜ ነው ብለዋል።
ወጣትና እያደገ ያለ የሰው ኃይል መኖሩ፣ ስትራቴጂካዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ፣ ጠንካራ የግብርና መሠረትና እየሰፋ ያለ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ዳይሬክተሯ ለኢትዮጵያ ተመራጭነት እንደ ምክንያት ጠቅሰዋል፡፡
በተጨማሪም ኢትዮጵያ በተስፋ ብቻ ሳትወሰን በተግባር የሚታዩ የሪፎርም እርምጃዎችን እየወሰደች በመሆኗ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...
Feb 24, 2025
ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...
Feb 24, 2025