የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

ኢንስቲትዩቱ የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ ምርምሮችን እያከናወነ ነው

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ የካቲት 27/2018(ኢዜአ)፦ የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት የህዝብ ባህል፣ ታሪክና እሴት ላይ ዘርፈ ብዙ የጥናትና ምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ።

የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ አስራት እንደገለጹት፤ ተቋሙ በኦሮሞ ባህል፣ እሴት፣ ስነ-ጥበብ፣ ታሪክ፣ ቋንቋና እድገት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ይገኛል።

ወጣቶች መልካም ስብዕናን ተላብሰው ለሀገር ልማት እና እድገት እንዲተጉ የባለድርሻ አካላት ሚና ሊጠናከር ይገባል

ይህንንም ውጤታማ ለማድረግ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ እና በክልሉ ከሚገኙ ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ከቱሪዝም ኮሚሽን፣ ከባህል ጥናት ማዕከል እንዲሁም ከወጣቶችና ስፖርት ቢሮዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ እስካሁን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ከ70 በላይ የምርምር ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።

ከእነዚህም መካከል በታሪክ፣ በቋንቋና በባህል ላይ ያተኮሩ ከ30 በላይ መጻሕፍት ታትመው ለማህበረሰቡ ተደራሽ ሆነዋል ብለዋል።


እነዚህ ስራዎች በተለይም የወጣቶችን የማንበብ ባህል ለማጠናከርና ሁለንተናዊ ስብዕናቸው እንዲገነባ ለማስቻል ትልቅ ድርሻ እንዳላቸውም አመልክተዋል።

የጥናት ውጤቶቹንና የመጻሕፍት ዝግጅቱን አስመልክቶ አስተያየታቸውን የሰጡ ወጣቶች፣ ስራው በትውልዱ ላይ የሚታየውን የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላት እንደሚረዳ ገልጸዋል።


ወጣት ስራጅ አህመድ እንደገለጸው፣ ንባብ ወጣቶች ስለ ማህበረሰቡ ስብዕናና ባህል እንዲያውቁ ያደርጋል።

የገዳ ስርዓት መሰረታችንና ማንነታችን ነው ያለው ወጣት ስራጅ፣ ስለ ስርዓቱና ስለ ኦሮሞ እሴቶች በቂ እውቀት ለማግኘት የንባብ ባህላችንን ማጎልበት ይገባናል ብሏል።

ተተኪው ትውልድ ስራን ከመናቅ ወጥቶ በልማት ስራዎች ላይ በንቃት መሳተፍ እንዳለበትም ነው የገለጸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025