የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

አይቻልምን የሰበሩ የሰማይ ከዋክብት

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ወደ ሀገር ውስጥና ውጭ ሀገራት በሴቶች ብቻ የሚመሩ ስምንት በረራዎችን ያደርጋል።

ዓለም ዙሪያ ካሉ የንግድ አውሮፕላን አብራሪዎች መካከል የሴቶች ድርሻ እስከ ስድስት በመቶ የሚደርስ ብቻ መሆኑን መረጃዎች ያመላክታሉ።

ከዓለም አቀፉ አማካኝ የተሻለ ቁጥር ከያዙት መካከል የህንድ አየር መንገድ ኤር ኢንዲያ ከጠቅላላ አብራሪዎቻቸው ውስጥ እስከ 15 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው።

የኢትዮጵያ አየር መንገድም አሁን ላይ 95 ሴት አብራሪዎች ያሉት ሲሆን፣ ቁጥሩን በፍጥነት እያሳደጉ ካሉ ጥቂት የአፍሪካ አየር መንገዶች በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው።


ኢዜአ ያነጋገራቸው በበረራው የተሳተፉ ሴት ረዳት አብራሪዎች በሴቶች ብቻ በሚመራ በረራ መሳተፍ ኩራትም ደስታም የሚፈጥር መሆኑን ይገልፃሉ።

ረዳት አብራሪ ፅዮን ደመቀ እንዳሉት በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ወጣት ሴት አውሮፕላን አብራሪ ካፒቴን አምሳለ ጓሉን በማየትና በመነሳሳት ዘርፉን ተቀላቅለዋል።

ዘርፉን ከተቀላቀሉ ወዲህ በሚሄዱባቸው ቦታዎች ሁሉ የሚመለከቷቸው ሰዎች ማበረታቻ እንደሚሰጧቸውም ተናግረዋል።


ሌላዋ ረዳት አብራሪ ሊዲያ ጋሜ በበኩላቸው ዘርፉ ለሴት ልጅ ይፈትናሉ ተብለው ከሚታሰቡ መካከል ቢሆንም ሴት ልጅ እንደምትችል ካሳዩ ቀደምቶቻችን በመማር ዘርፉን ተቀላቅለናል ብለዋል።

በሴቶች ብቻ በተመራ በረራ ላይ ተሳታፊ መሆናቸው ደስታና ኩራትን ያጎናፀፋቸው መሆኑንም ረዳት አብራሪዎቹ ገልፀዋል።

በትጋት ጠንክሮ በመስራት የሚኖሩ ችግሮችን በድልና በተስፋ ማለፍ የስኬት ቁልፍ ነው ያሉት አብራሪዎቹ ሴቶች የአልችልምን መንፈስ ሰብረው የራስ መተማመንን ካጎለበቱ የፈለጉት ቦታ ይደርሳሉ ሲሉም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025