የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በዞኑ የሌማት ትሩፋት ተሳታፊዎች ምርታቸውን ከፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ ሆነዋል

Mar 9, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጊምቢ ፤ የካቲት 28/2018 (ኢዜአ)፦በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በመሳተፍ ምርታቸውን ከቤተሰብ ፍጆታ ባለፈ ለገበያ በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉ መሆኑን በምዕራብ ወለጋ ዞን ቤጊ ወረዳ የሚገኙ ወጣቶችና ሴቶች ገለጹ።

በዞኑ የእንስሳት ዝርያን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የማሳደግ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት በበኩሉ በበጀት ዓመቱ መርሃ ግብሩን ለማስፋፋትና ለማጠናከር ከ3 ሚሊዮን በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችና ቄብ ዶሮዎች፣ 100 ሺህ የሚጠጋ ዘመናዊ የንብ ቀፎ ማሰራጨቱን አስታውቋል።

በቤጊ ወረዳ የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች መካከል እስራኤል ብሩሴና ዮሐንስ ዘሪሁን ለኢዜአ በሰጡት አስተያየት፤ በማህበር ተደራጅተው በሌማት ትሩፋት የተሻሻሉ የወተት ላም ዝርያ በማርባት ተጠቃሚ ሆነዋል።


እንደ ወጣቶቹ አስተያየት እያረቧቸው ካሉት የተሻሻሉ አምስት የወተት ላሞች በቀን ከ50 ሊትር በላይ ወተት ያመርታሉ።

ምርቱንም ከቤተሰብ ፍጆታ ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የተሻለ ገቢ እያገኙ መሆናቸውን ነው የተናገሩት።

በተለይ የወተት ምርቱን በወረዳው ለሚገኙ ሆቴሎች፣ ካፌዎችና ነዋሪዎች በተመጣጣኝ ዋጋ ስለሚያቀርቡ የገበያ ችግር እንዳላጋጠማቸው ገልጸው ከሽያጩም በወር በአማካኝ ከ25 ሺህ እስከ 30 ሺህ ብር የተጣራ ትርፍ እንደሚያገኙ አስረድተዋል።

ገቢያቸውን በመቆጠብና ሥራቸውን በማስፋፋት ለሌሎች የአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ዕቅድ እንዳላቸውም አስታውቀዋል።


በቤጊ ወረዳ የኮቦር ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ዘነበች ዲቢሳ በኩላቸው፤ በሌማት ትሩፋት የዶሮ ጫጩት ማሳደግ እና ማከፋፈል ሥራ ላይ በማህበር ተደራጅተው ወደ ሥራ መግባታቸውን ይናገራሉ።

በከተማ አስተዳደሩ በተደረገላቸው የሼዶች ድጋፍ አሁን ላይ አንድ ሺህ የአንድ ቀን ጫጩቶችን ተረክበው በማሳደግ ላይ እንደሚገኙ ጠቁመው በቀጣይ እንቁላል ጣይ ዶሮዎችን በማርባት ተጠቃሚነታቸውን ለማስፋት እየሠሩ መሆናቸውን አብራርተዋል።


የምዕራብ ወለጋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፈይሳ ሀምቢሳ፤ በዞኑ የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተግባራዊ በመሆኑ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ አስተዋፅኦ ከማበርከቱ ባለፈ ለብዙዎች የኢኮኖሚ ምንጭ በመሆን በተጨባጭ ውጤት ማስገኘቱን አውስተዋል።

ጽሕፈት ቤቱ ልማቱን ለማጠናከርና ለማስፋፋት የዶሮ ጫጩቶች፣ የተሻሻሉ ዝርያ ያላቸው የወተት ላሞችና የንብ ቀፎ ለመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች ማቅረቡን አመልክተዋል፡፡

በዚህ ረገድ በተያዘው በጀት ዓመት ብቻ በዶሮ እርባታ ለተሰማሩ ነዋሪዎች 3 ሚሊዮን 250 ሺህ በላይ የአንድ ቀን ጫጩቶችና ቄብ ዶሮዎች፣ 100 ሺህ የሚጠጋ ዘመናዊ የንብ ቀፎ መሰራጨቱን ገልጸዋል።

ከዚህ በፊት የተሰራጩ የተሻሻሉ ጊደሮችን በሰው ሠራሽ ዘዴ በማዳቀልም 24 ሺህ ጥጆች ተወልደው እንክብካቤ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025

<p>በዲጂታል አሰራር አማካኝነት የግዥ ስርዓቱን ዓለም አቀፋዊ፣ ግልፅና አሳታፊ ማድረግ ተችሏል</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ባለፉት ስድስት ዓመታት የፋይናንስ ዘርፉንና የመንግስት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል አሰራር በመቀየር የግዥ ስርዓቱን ዓ...

Feb 28, 2025

<p>ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት ነው - ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የቀጣናውን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ፕሮጀክት መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳን...

Feb 24, 2025

<p>በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል</p>

ጋምቤላ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል በቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የዜጎችን ተጠቃሚነት እውን ያደረጉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብ...

Feb 24, 2025