የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሎቹ የከተሞች አገልግሎት አሰጣጥን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር ውጤት እያመጣ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የከተሞች አገልግሎት አሰጣጥን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር ውጤት እያመጣ መሆኑ ተገለጸ።

የክልሎቹ የዘርፍ የስራ ኃላፊዎች ለኢዜአ እንደገለጹት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የተገልጋይነት እርካታን ለማሳደግ በትኩረት ሲሰራ ቆይቷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተማና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጨምር ኃይሌ እንደገለጹት፤ በክልሉ የአገልግሎት አሰጣጡን ከወረቀት ንክኪ ነፃ በማድረግ ወደ ዲጂታል ስርዓት ለማስገባት ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል።

በተለይም በመሬት፣ በግንባታ ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር እንዲሁም የገቢዎችን ዘርፍ ጨምሮ 55 የሚሆኑ አገልግሎቶች በዲጂታል መንገድ መሰጠት መጀመሩን ተናግረዋል።

የዲጂታል አገልግሎቱ በመጀመሪያው ምዕራፍ በሆሳዕና፣ በቡታጂራ፣ በወልቂጤ፣ በዱራሜ፣ በወራቤ፣ በአላባ ቁሊቶና በሳጃ ከተሞች የተጀመረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በ16 ከተሞች በዲጂታል ዘዴ የታገዘ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይም በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥን ወደ 24 ከተሞች ለማሳደግ የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ብለዋል።

አቶ ጨምር አክለውም የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሶፍትዌሮችን በማቅረብ እና የዲጂታላይዜሽን ስራውን በማስፋፋት ረገድ ትልቅ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።

ይህም የመረጃ አያያዝን ከማዘመኑም ባለፈ፣ ፋይል ለመፈለግ ይባክን የነበረውን ጊዜና የተገልጋዮችን ቅሬታ መቀነስ መቻሉን፣ እንዲሁም የሊዝ እዳ መረጃን በአግባቡ ለማወቅና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል።


በተመሳሳይም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ የከተማ ልማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር ቢፍቱ ጎሹ፤ በክልሉ ከተሞች የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በመሬት እና በገቢዎች ዘርፍ ያሉ ፋይሎችን ወደ ሶፍት ኮፒ የመቀየር ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው የተቀናጀ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በስምንት ማዕከላት ለማስጀመር እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል።

በአሶሳ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ሙሉ በሙሉ ለመጀመር የግንባታና የፋይሎችን መረጃ ወደ ዲጂታል የማስገባት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ኢንጂነር ቢፍቱ አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል-ሰልጣኞች

አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...

Apr 29, 2026

በአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርዓትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድ የሚወሰድበት ነው

ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...

Apr 15, 2026

መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የፈጠራ ክህሎት ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነ ነው

ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...

Apr 14, 2026

<p>የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...

Feb 28, 2025