የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
አንድ ቀበቶ ፣ አንድ መንገድ

በክልሎቹ የከተሞች አገልግሎት አሰጣጥን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር ውጤት እያመጣ ነው

Mar 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፡- በማዕከላዊ ኢትዮጵያና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የከተሞች አገልግሎት አሰጣጥን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር ውጤት እያመጣ መሆኑ ተገለጸ።

የክልሎቹ የዘርፍ የስራ ኃላፊዎች ለኢዜአ እንደገለጹት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የተገልጋይነት እርካታን ለማሳደግ በትኩረት ሲሰራ ቆይቷል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተማና ኮንስትራክሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ጨምር ኃይሌ እንደገለጹት፤ በክልሉ የአገልግሎት አሰጣጡን ከወረቀት ንክኪ ነፃ በማድረግ ወደ ዲጂታል ስርዓት ለማስገባት ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል።

በተለይም በመሬት፣ በግንባታ ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር እንዲሁም የገቢዎችን ዘርፍ ጨምሮ 55 የሚሆኑ አገልግሎቶች በዲጂታል መንገድ መሰጠት መጀመሩን ተናግረዋል።

የዲጂታል አገልግሎቱ በመጀመሪያው ምዕራፍ በሆሳዕና፣ በቡታጂራ፣ በወልቂጤ፣ በዱራሜ፣ በወራቤ፣ በአላባ ቁሊቶና በሳጃ ከተሞች የተጀመረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በ16 ከተሞች በዲጂታል ዘዴ የታገዘ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይም በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥን ወደ 24 ከተሞች ለማሳደግ የተጀመረው ስራ ይጠናከራል ብለዋል።

አቶ ጨምር አክለውም የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሶፍትዌሮችን በማቅረብ እና የዲጂታላይዜሽን ስራውን በማስፋፋት ረገድ ትልቅ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።

ይህም የመረጃ አያያዝን ከማዘመኑም ባለፈ፣ ፋይል ለመፈለግ ይባክን የነበረውን ጊዜና የተገልጋዮችን ቅሬታ መቀነስ መቻሉን፣ እንዲሁም የሊዝ እዳ መረጃን በአግባቡ ለማወቅና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል።


በተመሳሳይም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ የከተማ ልማት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ኢንጂነር ቢፍቱ ጎሹ፤ በክልሉ ከተሞች የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በመሬት እና በገቢዎች ዘርፍ ያሉ ፋይሎችን ወደ ሶፍት ኮፒ የመቀየር ስራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰው የተቀናጀ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በስምንት ማዕከላት ለማስጀመር እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል።

በአሶሳ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ሙሉ በሙሉ ለመጀመር የግንባታና የፋይሎችን መረጃ ወደ ዲጂታል የማስገባት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ኢንጂነር ቢፍቱ አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ታዋቂው ታይም መጽሔት ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባስነበበው ሰፊ ዘገባው ምን አለ?

በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...

Sep 14, 2026

የኦሮሚያ ክልል ንግድ ቢሮ ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ትኩረት ሰጥቷል

አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...

Sep 7, 2026

የመስኖና የሜካናይዜሽን ሽግግር በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ ከተመዘገቡት ስኬቶች ዋነኞቹ ናቸው-ምሁራን

ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...

Sep 3, 2026

በአማራ ክልል የጥጥ ምርትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል

ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...

Aug 28, 2026