🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦በዝምባብዌ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሉክ ማላባ የተመራ የሀገሪቷ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን ጎብኝቷል።
የተቀናጀ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት የዜጎች ተጠቃሚነት ማጎልበቻ ሆነዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
በዚህም በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የስራ ሀላፊዎች ለጎብኚዎቹ ገለጻና ማብራሪያ ተደርጎላቸዋል።

የዝምባብዌ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሉክ ማላባ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በሕግ ዘርፍ ውስጥ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው በጉብኝታቸው ወቅት ገልጸዋል።
አገራቸው የፍትሕ ሥርዓቱን ውጤታማነትና ቅልጥፍና ለማሳደግ ቴክኖሎጂን ለመጠቀም ያላትን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።
ቴክኖሎጂን መጠቀም የፍርድ ቤቶችን የአሠራር ቅልጥፍና ከማሳደጉም በላይ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እንደሚረዳ ጠቁመዋል።
በዚህ ረገድ፣ ጉብኝቱ የልዑካን ቡድኑ ከኢትዮጵያ የፍትሕ ሥርዓት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሂደትና ተሞክሮ እንዲማሩ ትልቅ ዕድል እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።

በተጨማሪም የዝምባብዌ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ቴዎድሮስ ምህረት እና የዝምባብዌ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሉክ ማላባ ተፈራርመውታል።
አሶሳ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦ ከስልጠናው ያገኘነው እውቀት ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ የህብረት ስራ ማህበራትን ለመፍጠር ያግዘናል ሲሉ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክ...
Apr 29, 2026
ባህርዳር ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- የአማራ ክልል በቴክኖሎጂ የታገዘ የገቢ አሰባሰብ ስርአትን በመተግበር ረገድ የተገኘው ውጤት ልምድና ተሞክሮ የሚወሰድበት...
Apr 15, 2026
ሮቤ፣ ሚያዝያ 5/2018 (ኢዜአ)፦ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዝንባሌ ያላቸው ተማሪዎችን ለተሻለ ውጤት ማብቃት የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወ...
Apr 14, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የስንዴ ልማት ስራዎችን ለማስፋት መንግስት በትኩረት እየሰራ ነው ሲሉ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገ...
Feb 28, 2025