🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 1/2018(ኢዜአ)፦በዝምባብዌ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሉክ ማላባ የተመራ የሀገሪቷ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን ጎብኝቷል።
የተቀናጀ የአገልግሎት መስጫ ማዕከላት የዜጎች ተጠቃሚነት ማጎልበቻ ሆነዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
በዚህም በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የስራ ሀላፊዎች ለጎብኚዎቹ ገለጻና ማብራሪያ ተደርጎላቸዋል።

የዝምባብዌ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሉክ ማላባ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በሕግ ዘርፍ ውስጥ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው በጉብኝታቸው ወቅት ገልጸዋል።
አገራቸው የፍትሕ ሥርዓቱን ውጤታማነትና ቅልጥፍና ለማሳደግ ቴክኖሎጂን ለመጠቀም ያላትን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።
ቴክኖሎጂን መጠቀም የፍርድ ቤቶችን የአሠራር ቅልጥፍና ከማሳደጉም በላይ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እንደሚረዳ ጠቁመዋል።
በዚህ ረገድ፣ ጉብኝቱ የልዑካን ቡድኑ ከኢትዮጵያ የፍትሕ ሥርዓት የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ሂደትና ተሞክሮ እንዲማሩ ትልቅ ዕድል እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።

በተጨማሪም የዝምባብዌ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በጋራ መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ቴዎድሮስ ምህረት እና የዝምባብዌ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሉክ ማላባ ተፈራርመውታል።
በታዋቂው ታይም መጽሔት (TIME Magazine) ላይ እንግሊዛዊው ጸሐፊ ጆሽ ዊልሰን “THE POWER TO UNITE AFRICA” (አፍሪካን የማስተሳሰር ኃይል)...
Sep 14, 2026
አዳማ፤ጳጉሜን1/2018(ኢዜአ)-መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ በፍጆታ ምርቶች ላይ የዋጋ ንረት እንዳይከሰት ለመከላከል ትኩረት መሰጠቱን የኦሮ...
Sep 7, 2026
ጅማ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ):- ከዝናብ ጥገኝነት በመላቀቅ ወደ መስኖ ልማትና ሜካናይዜሽን እየተደረገ ያለው ሽግግር፣ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ አዲስ ምዕራፍ...
Sep 3, 2026
ባህር ዳር፤ ነሐሴ 21/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የጥጥ ልማትን በጥራትና በብዛት በማምረት ለጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪዎች በግብአትነት ለማቅረብ ልዩ ትኩረት ...
Aug 28, 2026